News

National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በጣሊያን ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት የተማራ ልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፊሰር ብርሃኑ ነጋ በጣሊያን ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA የተመራ ልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ በአገሪቱ ትምህርትን በጥራትና በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የሪፎርም ተግባራት ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
በቀደመው ጊዜ ትምህርትን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ሰፊ ሥራ ቢሰራም የትምህርት ጥራት ተዘንግቶ መቆየቱን ጠቅሰው ይህንንም ከመሰረቱ ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርጸው እየተተገበሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በትምህርት ስርዓቱ የተበላሸውን የሞራል መሰረት ለማስተካከል ሥርዓተ ትምህርቱን ከመቀየር ጀምሮ የፈተና አስተዳደር ስረዓቱን ከስርቆትና ኩረጃ በጸዳ መልኩ በመስጠት የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
ስታንዳርዳቸውን ያሟሉ ትምህርት ቤቶች በጣም ጥቂት መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ከ17 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉንም አንስተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የተማሪ መጽሃፍትን በሁለተኛ ደረጃ አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉንና ከአለም አቀፍ ትብብር ለትምህርት በተገኘ ድጋፍ ተጨማሪ መጽሃፍትን ለአንደኛ ደረጃ ለማሳተምና ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን አብራርተው የጣሊያን መንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የጣሊያን የምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA በበኩላቸው ጣሊያን በኢትዮጵያና በአፍሪካ በተለያዩ የልማት መስኮች ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተው በቀጣይ የዓለም አቀፉ ትብብር ለትምህርት (GPE) መሪነት እንደምትረከብና በዘርፉ ድጋፍ ማድረግ ፍላጎት እንዳላትም ገልጸዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየወሰደቻቸው ያሉ ሪፎርሞችን በአድናቆት እንደሚመለከቱት ገጸው ለተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ እደሚያደርጉ ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፊሰር ብርሃኑ ነጋ በጣሊያን ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA የተመራ ልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ በአገሪቱ ትምህርትን በጥራትና በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የሪፎርም ተግባራት ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
በቀደመው ጊዜ ትምህርትን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ሰፊ ሥራ ቢሰራም የትምህርት ጥራት ተዘንግቶ መቆየቱን ጠቅሰው ይህንንም ከመሰረቱ ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርጸው እየተተገበሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በትምህርት ስርዓቱ የተበላሸውን የሞራል መሰረት ለማስተካከል ሥርዓተ ትምህርቱን ከመቀየር ጀምሮ የፈተና አስተዳደር ስረዓቱን ከስርቆትና ኩረጃ በጸዳ መልኩ በመስጠት የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
ስታንዳርዳቸውን ያሟሉ ትምህርት ቤቶች በጣም ጥቂት መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ከ17 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉንም አንስተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የተማሪ መጽሃፍትን በሁለተኛ ደረጃ አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉንና ከአለም አቀፍ ትብብር ለትምህርት በተገኘ ድጋፍ ተጨማሪ መጽሃፍትን ለአንደኛ ደረጃ ለማሳተምና ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን አብራርተው የጣሊያን መንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የጣሊያን የምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA በበኩላቸው ጣሊያን በኢትዮጵያና በአፍሪካ በተለያዩ የልማት መስኮች ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተው በቀጣይ የዓለም አቀፉ ትብብር ለትምህርት (GPE) መሪነት እንደምትረከብና በዘርፉ ድጋፍ ማድረግ ፍላጎት እንዳላትም ገልጸዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየወሰደቻቸው ያሉ ሪፎርሞችን በአድናቆት እንደሚመለከቱት ገጸው ለተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ እደሚያደርጉ ተናግረዋል።
Aug 01, 2025 26
National News

ትምህርት ለሀገር እድገት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ የዘርፍ ባለሙያዎች ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ፣ የተቋሙን ተልዕኮ በሚገባ የሚፈጽሙና የሚያስፈጽሙ ሊሆኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አሳሰቡ።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች በሚኒስቴሩ እና በሀገራችን የ2017 እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም የልማት ዕቅድ እንዲሁም በተቋሙ እየተካሄዱ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞች ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ፣ዘመናዊና የተቋሙን ተልዕኮ በሚገባ የሚፈጽሙ አርኣያነት ያላቸው ሠራተኞች ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሰራተኞች የሚጠበቅባቸውን ተልዕኮ በቅንነትና በብቃት እንዲወጡ ምቹ የሥራ አካባቢ መኖር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም ለማሳካት በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በውይይት መድረኩ የሀገሪቱን የ2018 ዓ.ም የልማት እቅድ ባቀረቡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች የሀገርና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለተጀመሩ ተስፋ ሰጪ የለውጥና ዓበይት ሥራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አንስተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም ጥሩ ውጤት የተመዘገበባቸውን ሥራዎች አስጠብቆ ማስቀጠልና ዝቅተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው ሥራዎችን በልዩ ሁኔታ በመያዝ በቀጣይ በጀት ዓመት በትኩረት እንደሚገባ አጽናኦት ሰጥተዋል፡፡
የሚኒስቴሩ ሰራተኞችም በቀረቡ ሰነዶች ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች በሚኒስቴሩ እና በሀገራችን የ2017 እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም የልማት ዕቅድ እንዲሁም በተቋሙ እየተካሄዱ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞች ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ፣ዘመናዊና የተቋሙን ተልዕኮ በሚገባ የሚፈጽሙ አርኣያነት ያላቸው ሠራተኞች ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሰራተኞች የሚጠበቅባቸውን ተልዕኮ በቅንነትና በብቃት እንዲወጡ ምቹ የሥራ አካባቢ መኖር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም ለማሳካት በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በውይይት መድረኩ የሀገሪቱን የ2018 ዓ.ም የልማት እቅድ ባቀረቡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች የሀገርና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለተጀመሩ ተስፋ ሰጪ የለውጥና ዓበይት ሥራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አንስተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም ጥሩ ውጤት የተመዘገበባቸውን ሥራዎች አስጠብቆ ማስቀጠልና ዝቅተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው ሥራዎችን በልዩ ሁኔታ በመያዝ በቀጣይ በጀት ዓመት በትኩረት እንደሚገባ አጽናኦት ሰጥተዋል፡፡
የሚኒስቴሩ ሰራተኞችም በቀረቡ ሰነዶች ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Jul 31, 2025 20
National News

ተባብረን በመትከል ለልጆቻችን አረንጓዴ ሀገር እናስረክባለን፤ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች 700 ሚሊየን የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ የግንፍሌ ወንዝ ዳር ፕሮጀክት አስቀምጠዋል።
በምርሃ ግብሩ ተገኝተው አሻራቸውን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተባብረን በመትከል ለልጆቻችን አረንጓዴ ሀገር እናስረክባለን ያሉ ሲሆን የጎዳናትን ፕላኔት ጥሩ ስራ ሰርተን ምቹ የሰው ልጆች መኖሪያ ለማድረግ መትጋት አለብን ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮች ችግኝ በአንድ ጀንበር የሚለው መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስታ እንደፈጠረባቸው ጠቁመው የሚተከሉት ችግኞች ጸድቀው ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊው እንክብካቤ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
የተተከሉት ችግኞች የአየር ሚዛንን በመጠበቅ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ እንደሚሆንም አክለዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ የሚተከሉት ችግኞች ለአካባቢውን ውበት እንደሚጨምሩ ገልጸው በዚህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስ እንዳሰኛቸው ተናግረዋል።
 
 
 
 
 
 
 
ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች 700 ሚሊየን የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ የግንፍሌ ወንዝ ዳር ፕሮጀክት አስቀምጠዋል።
በምርሃ ግብሩ ተገኝተው አሻራቸውን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተባብረን በመትከል ለልጆቻችን አረንጓዴ ሀገር እናስረክባለን ያሉ ሲሆን የጎዳናትን ፕላኔት ጥሩ ስራ ሰርተን ምቹ የሰው ልጆች መኖሪያ ለማድረግ መትጋት አለብን ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮች ችግኝ በአንድ ጀንበር የሚለው መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስታ እንደፈጠረባቸው ጠቁመው የሚተከሉት ችግኞች ጸድቀው ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊው እንክብካቤ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
የተተከሉት ችግኞች የአየር ሚዛንን በመጠበቅ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ እንደሚሆንም አክለዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ የሚተከሉት ችግኞች ለአካባቢውን ውበት እንደሚጨምሩ ገልጸው በዚህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስ እንዳሰኛቸው ተናግረዋል።
 
 
Jul 31, 2025 16
National News

ኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 2ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም ያላትን ልምድ አካፈለች።

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 2ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም አተገባበር ያላትን ልምድና የመንግስትን ቁርጠኝነት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አቅርበዋል።
የሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ፖሊሲ ፍሬም ዎርክ በማውጣት ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተግባራዊ በማድረግ የአካባቢ ልማትና ግብርናን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በዚህ የሀገር በቀል የት/ቤት ምገባ ፕሮግራም መንግስት 6.3 ቢሊየን ብርመመደቡንና የማህበረሰቡ ድጋፍ ደግሞ 9.8 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጸው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ ደግሞ 1.3 ቢሊየን መሆኑን አብራርተዋል።
ይህም በኢትዮጵያ ለት/ቤት ምገባ 90 በመቶ የሚደርሰው በጀት በመንግስትና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚሸፈን መሆኑን ገልጸው ተግባሩ የመንግስትንና የማህበረሰቡን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምገባ ፕሮግራሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህፃናት ትምህርታቸው ላይ ትኩረት አድረገው እንዲማሩ ከማድረጉ ባለፈ፤ ጤንነታቸው ተጠብቆ ትምህርታቸው ሳይቋረጥ እንዲማሩ ማድረግ ያስቻለ ተግባር ስለመሆኑም ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከአለም የትምህርት ቤት ምግብ ጥምረት (School Meal Coalition) እና ከአለም የምግብ ፕሮግራም ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
 
 
 
 
በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 2ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም አተገባበር ያላትን ልምድና የመንግስትን ቁርጠኝነት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አቅርበዋል።
የሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ፖሊሲ ፍሬም ዎርክ በማውጣት ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተግባራዊ በማድረግ የአካባቢ ልማትና ግብርናን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በዚህ የሀገር በቀል የት/ቤት ምገባ ፕሮግራም መንግስት 6.3 ቢሊየን ብርመመደቡንና የማህበረሰቡ ድጋፍ ደግሞ 9.8 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጸው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ ደግሞ 1.3 ቢሊየን መሆኑን አብራርተዋል።
ይህም በኢትዮጵያ ለት/ቤት ምገባ 90 በመቶ የሚደርሰው በጀት በመንግስትና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚሸፈን መሆኑን ገልጸው ተግባሩ የመንግስትንና የማህበረሰቡን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምገባ ፕሮግራሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህፃናት ትምህርታቸው ላይ ትኩረት አድረገው እንዲማሩ ከማድረጉ ባለፈ፤ ጤንነታቸው ተጠብቆ ትምህርታቸው ሳይቋረጥ እንዲማሩ ማድረግ ያስቻለ ተግባር ስለመሆኑም ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከአለም የትምህርት ቤት ምግብ ጥምረት (School Meal Coalition) እና ከአለም የምግብ ፕሮግራም ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
 
 
 
 
Jul 29, 2025 15
National News

የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ የበጎ ተግባራት መገለጫ በተለይም መተጋገዝን፣ መደጋገፍን፣ መረዳዳትንና መከባበር የበለጠ ለማላቅ እድል የሚሰጥ ነው፤ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ፤ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች በጋምቤላ ክልል ተገኝተው የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን አስጀምረዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማት እና የዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ አመራሮች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል ተገኝተው አስጀምረዋል።
በክረምት የበጎ ፍቃድ ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ የሀገርን ገጽታ የቀየሩ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን በተለይም የአረንጓዴ አሻራና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቅሰው ሁለተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተጋች ባለች ሀገር እርስ በርስ መተጋገዝና መደጋገፍ ይገባናል ብለዋል።
አክለውም ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል በማስጀመራቸው ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን ሀሳብ አመንጭነት ባልፉት ዓመታት ሲተገብር የቆየው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበጎ ተግባራት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም መተጋገዝን፣ መደጋገፍን፣ መረዳዳትንና መከባበር የበለጠ ለማላቅ እድል የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ሁሉም ኃላፊነቱን በሚገባ ከተወጣ ኢትዮጵያ የያዘችውን የብልጽግና ጉዞ ለሁሉም እኩል እድል በመስጠት ለማሳካት ትልቅ አቅም ይሆናል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር፣ ተጠሪ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በጋምቤላ ክልል ባስጀመሩት በዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ፣ ችግር ላለባቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እና በመትከል ማንሰራራ በሚል ዘንድሮ በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማት እና የዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ አመራሮች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል ተገኝተው አስጀምረዋል።
በክረምት የበጎ ፍቃድ ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ የሀገርን ገጽታ የቀየሩ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን በተለይም የአረንጓዴ አሻራና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቅሰው ሁለተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተጋች ባለች ሀገር እርስ በርስ መተጋገዝና መደጋገፍ ይገባናል ብለዋል።
አክለውም ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል በማስጀመራቸው ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን ሀሳብ አመንጭነት ባልፉት ዓመታት ሲተገብር የቆየው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበጎ ተግባራት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም መተጋገዝን፣ መደጋገፍን፣ መረዳዳትንና መከባበር የበለጠ ለማላቅ እድል የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ሁሉም ኃላፊነቱን በሚገባ ከተወጣ ኢትዮጵያ የያዘችውን የብልጽግና ጉዞ ለሁሉም እኩል እድል በመስጠት ለማሳካት ትልቅ አቅም ይሆናል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር፣ ተጠሪ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በጋምቤላ ክልል ባስጀመሩት በዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ፣ ችግር ላለባቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እና በመትከል ማንሰራራ በሚል ዘንድሮ በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
Jul 29, 2025 19
National News

የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በመጪው የትምህርት ዘመን እንደሚተገበር ተገለጸ።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል በ2018 ዓ.ም አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በ6 ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
‎የመርሃ ግብሩ ዓላማ የመምህራንን አጠቃላይ አቅርቦት በማሻሻል ረገድ የሚስተዋሉ እጥረቶችና የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት መሆኑንም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
‎በአማራጭ የመምህራን የትምህርት መርሃ ግብሩ ከምሁራን ጋር የተመከረበት ፣ በየደረጃው የሚገኙ መምህራንና ሌሎችም የዘርፉ ባለድርሻዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በውይይት ከዳበረ በኋላ መጽደቁን አብራርተዋል።
‎አማራጭ የመምህራን ትምህርት መርሃ ግብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተገበር ከአሁን በፊት በትምህርት ዙሪያ በትኩረት እንዲሰሩ በተለዩ 6 ዩኒቨርስቲዎችና ክልሎች መላኩን ጠቁመዋል።
‎ከሁለተኛ ደረጃ መምህራን አቅርቦት ባሻገርም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ላይ ያለውን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል ፕሮግራሙ እንደ አንድ አማራጭ እንዲወሰድ ፍሬም ዎርኩ ለክልሎች እንዲደርስ መደረጉንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ጨምረው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራሙ የመምህራንን አቅርቦት ለማሳደግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎ፕሮግራሙ በመጪው የትምህርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ላይ በሚሰሩ 6ቱ ዩኒቨርስቲዎች የሚተገበር ቢሆንም ውጤቱ እየታየ እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድም ሃላፊው አክለው ገልጸዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል በ2018 ዓ.ም አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በ6 ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
‎የመርሃ ግብሩ ዓላማ የመምህራንን አጠቃላይ አቅርቦት በማሻሻል ረገድ የሚስተዋሉ እጥረቶችና የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት መሆኑንም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
‎በአማራጭ የመምህራን የትምህርት መርሃ ግብሩ ከምሁራን ጋር የተመከረበት ፣ በየደረጃው የሚገኙ መምህራንና ሌሎችም የዘርፉ ባለድርሻዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በውይይት ከዳበረ በኋላ መጽደቁን አብራርተዋል።
‎አማራጭ የመምህራን ትምህርት መርሃ ግብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተገበር ከአሁን በፊት በትምህርት ዙሪያ በትኩረት እንዲሰሩ በተለዩ 6 ዩኒቨርስቲዎችና ክልሎች መላኩን ጠቁመዋል።
‎ከሁለተኛ ደረጃ መምህራን አቅርቦት ባሻገርም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ላይ ያለውን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል ፕሮግራሙ እንደ አንድ አማራጭ እንዲወሰድ ፍሬም ዎርኩ ለክልሎች እንዲደርስ መደረጉንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ጨምረው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራሙ የመምህራንን አቅርቦት ለማሳደግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎ፕሮግራሙ በመጪው የትምህርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ላይ በሚሰሩ 6ቱ ዩኒቨርስቲዎች የሚተገበር ቢሆንም ውጤቱ እየታየ እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድም ሃላፊው አክለው ገልጸዋል።
Jul 24, 2025 517
National News

ኢትዮጵያና አልጄሪያ በትምህርትና ስልጠና መስክ ያላቸውን ትብብር ሊያሳድጉ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር መሀመድ ካሊድን በ/ጽቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
ሚንስትሩ ከአምባሰደሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ እየተለወጠ ባለው የአለም ስርዓት ውስጥ አፍሪካውያን ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን በትምህርት ዘርፍ ከአልጄሪያ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው ባረጉት ገለጻ በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን በጋራ ለመስራት ፣የመምህራንና ተማሪዎች ልውውጥ ለማድረግ ፣ የነጻ ትምህርት እድሎችን ለማመቻቸት እንዲሁም የቴክክና ሙያ ትምህርት አሰልጣኞች ስልጠና ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ዶ/ር መሀመድ ካሊድ በበኩላቸው ኢትዮጵና አልጀሪያ በቀጠናዊና አለማቀፋዊ የገራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትብብር ያላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህን ዘርፈ ብዙ ትብብር ማስፋትና ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
አምባሳደሩ በማያያዝ እንደገለጹት የአልጄሪያ መንግስት በኢትዮያ በኩል የሚቀርብለትን የትብብር ፍላጎት መሰረት በማድረግ ስምምነት የመፈራረምና አብሮ የመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር መሀመድ ካሊድን በ/ጽቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
ሚንስትሩ ከአምባሰደሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ እየተለወጠ ባለው የአለም ስርዓት ውስጥ አፍሪካውያን ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን በትምህርት ዘርፍ ከአልጄሪያ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው ባረጉት ገለጻ በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን በጋራ ለመስራት ፣የመምህራንና ተማሪዎች ልውውጥ ለማድረግ ፣ የነጻ ትምህርት እድሎችን ለማመቻቸት እንዲሁም የቴክክና ሙያ ትምህርት አሰልጣኞች ስልጠና ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ዶ/ር መሀመድ ካሊድ በበኩላቸው ኢትዮጵና አልጀሪያ በቀጠናዊና አለማቀፋዊ የገራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትብብር ያላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህን ዘርፈ ብዙ ትብብር ማስፋትና ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
አምባሳደሩ በማያያዝ እንደገለጹት የአልጄሪያ መንግስት በኢትዮያ በኩል የሚቀርብለትን የትብብር ፍላጎት መሰረት በማድረግ ስምምነት የመፈራረምና አብሮ የመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
Jul 23, 2025 281
National News

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ብቃትና ተነሳሽነት ለትምህርት ጥራት ወሳኝ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አስገነዘቡ፤

ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ከ84 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ።
‎የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የተጀመረውን የአሰልጣኞች ስልጠና ሲከፍቱ እንደገለጹት የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል።
መምህርነት ዜጋን በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነምግባር በማነጽ ተምህርት የሚያስጨብጥና ዜጎች ችግር ፈቺ ፣ተመራማሪ፣ ሀገር ተረካቢና ገንቢ እንዲሆኑ የሚቀርጽ ሙያ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎መምህርነት ቅድመ ሁኔታዎች ሳይገድቡት የወላጅነትና የባለአደራነት ሚና የሚወጣ የሙያዎች ሁሉ ቁንጮ በመሆኑ መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡና የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል የትምህርት ቤት አመራሮቾ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው ብለዋል።
‎የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሥርዓተ ትምህርት ፣በመምህራንና አመራሮች ልማት፣ትምህርት ቤቶችን ምቹ በማድረግና ሌሎች በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ ባለፈው ዓመት በተሰጠው ስልጠና ከተወሰዱ ልምዶች በመነሳት የታዩ ክፍተቶችን ሊቀርፉ የሚችሉ ስልቶችን በመንደፍ ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ለ2ኛ ጊዜ ከ84 ሺ ለሚበልጡ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና እንደሚሰጥ የገለፁ ሲሆን የዛሬው የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተሳታፊዎችም የተጣለባቸውን ትልቅ አገራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጡም የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው የትምህርት ስብራትን ለማከምና ትውልድን ለማነጽ መምህራን ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በበኩላቸው የአሰልጣኞች ስልጠናው ዓላማ የመምህራንንና የትምህርት አመራሮችን አቅምና ብቃት በማሳደግ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ መዘጋጀቱን ጠቁመው ባለፈው ዓመት የተሰጠው ስልጠና ጠቃሚ ልምድና ተሞክሮ መገኘቱንም አብራርተዋል።
‎ዛሬ በተጀመረውና ለሦስት ቀናት በሚቆየው ልዩ የክረምት መምህራንና የትምህርት አመራሮች የአሰልጣኞች ስልጠና ከ30 ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ 630 ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ከ84 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ።
‎የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የተጀመረውን የአሰልጣኞች ስልጠና ሲከፍቱ እንደገለጹት የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል።
መምህርነት ዜጋን በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነምግባር በማነጽ ተምህርት የሚያስጨብጥና ዜጎች ችግር ፈቺ ፣ተመራማሪ፣ ሀገር ተረካቢና ገንቢ እንዲሆኑ የሚቀርጽ ሙያ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎መምህርነት ቅድመ ሁኔታዎች ሳይገድቡት የወላጅነትና የባለአደራነት ሚና የሚወጣ የሙያዎች ሁሉ ቁንጮ በመሆኑ መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡና የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል የትምህርት ቤት አመራሮቾ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው ብለዋል።
‎የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሥርዓተ ትምህርት ፣በመምህራንና አመራሮች ልማት፣ትምህርት ቤቶችን ምቹ በማድረግና ሌሎች በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ ባለፈው ዓመት በተሰጠው ስልጠና ከተወሰዱ ልምዶች በመነሳት የታዩ ክፍተቶችን ሊቀርፉ የሚችሉ ስልቶችን በመንደፍ ከመጪው ሐምሌ 28 ጀምሮ ለ2ኛ ጊዜ ከ84 ሺ ለሚበልጡ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና እንደሚሰጥ የገለፁ ሲሆን የዛሬው የአሰልጣኞች ስልጠና መርሃ ግብር ተሳታፊዎችም የተጣለባቸውን ትልቅ አገራዊ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጡም የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው የትምህርት ስብራትን ለማከምና ትውልድን ለማነጽ መምህራን ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
‎የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በበኩላቸው የአሰልጣኞች ስልጠናው ዓላማ የመምህራንንና የትምህርት አመራሮችን አቅምና ብቃት በማሳደግ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ መዘጋጀቱን ጠቁመው ባለፈው ዓመት የተሰጠው ስልጠና ጠቃሚ ልምድና ተሞክሮ መገኘቱንም አብራርተዋል።
‎ዛሬ በተጀመረውና ለሦስት ቀናት በሚቆየው ልዩ የክረምት መምህራንና የትምህርት አመራሮች የአሰልጣኞች ስልጠና ከ30 ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ 630 ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
Jul 23, 2025 369
National News

"ለትውልድ ስንል አረንጎዴ አሻራችንን ያለልዩነት እናስቀምጣለን" የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሸገር ከተማ አካሄዱ።
"በመትከል ማንሠራራት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የአረንጎዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ለትውልድ ስንል አረንጓዴ አሻራችንን ያለልዩነት እናስቀምጣለን ብለዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በማያያዝ ባስተላለፉት መልእክት ሀገርና ትውልድን በሚጠቅሙ ጉዳዬች ላይ ሁሉም ዜጋ ያለልዩነት የበኩሉን አስተዋጾ ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የተከናወነው የችግኝ ተከላ ከስራና ሙያ ጋር የተያዘና ለተማሪዎች አርያ ለመሆን ታስቦ መሆኑን የገለጹትት ሚንስትሩ ሁሉም ዜጋ ባለው የሙያም ይሁን ማህበራዊ ትስስር ሁሌም አረንጓዴ አሻራውን ማኖር አለበት ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ሀገራችን እያከናወነች ያለው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሌሎች ሀገራት ልምድ የሚቀስሙበት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ልማቱ የተፈጥሮ ሚዛንን ከማስጠበቅ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጭምር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ለጋዜጠኞች በሠጡት ማብራሪያ ገልጸዋል።
አረንጓዴ አሻራን ማኖር አገራችን ኢትዮጵያን ወደፊት የሚወስድና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዋነኛ ተግባር በመሆኑ የሁልጊዜ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለትውልድ ምቹና ተስማሚ ሀገር ለማስረከብ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል።
መርሃ ግብሩ የአረንጎዴ አሻራ የሁሉም ነገር መሠረት ስለመሆኑ እንዲሁም አገርን ለማበልጸግና ወደፊት ለማሻገር ቁልፍ ሚና ያለው ስለመሆኑ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነው።
በመርሐ ግብሩ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የኢትዮጵይ ትምህርት ባለስልጣን እንዲሁም የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
 
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሸገር ከተማ አካሄዱ።
"በመትከል ማንሠራራት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የአረንጎዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ለትውልድ ስንል አረንጓዴ አሻራችንን ያለልዩነት እናስቀምጣለን ብለዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በማያያዝ ባስተላለፉት መልእክት ሀገርና ትውልድን በሚጠቅሙ ጉዳዬች ላይ ሁሉም ዜጋ ያለልዩነት የበኩሉን አስተዋጾ ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የተከናወነው የችግኝ ተከላ ከስራና ሙያ ጋር የተያዘና ለተማሪዎች አርያ ለመሆን ታስቦ መሆኑን የገለጹትት ሚንስትሩ ሁሉም ዜጋ ባለው የሙያም ይሁን ማህበራዊ ትስስር ሁሌም አረንጓዴ አሻራውን ማኖር አለበት ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ሀገራችን እያከናወነች ያለው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ሌሎች ሀገራት ልምድ የሚቀስሙበት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ልማቱ የተፈጥሮ ሚዛንን ከማስጠበቅ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ጭምር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ለጋዜጠኞች በሠጡት ማብራሪያ ገልጸዋል።
አረንጓዴ አሻራን ማኖር አገራችን ኢትዮጵያን ወደፊት የሚወስድና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዋነኛ ተግባር በመሆኑ የሁልጊዜ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለትውልድ ምቹና ተስማሚ ሀገር ለማስረከብ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አብራርተዋል።
መርሃ ግብሩ የአረንጎዴ አሻራ የሁሉም ነገር መሠረት ስለመሆኑ እንዲሁም አገርን ለማበልጸግና ወደፊት ለማሻገር ቁልፍ ሚና ያለው ስለመሆኑ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነው።
በመርሐ ግብሩ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የኢትዮጵይ ትምህርት ባለስልጣን እንዲሁም የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
 
Jul 22, 2025 306
National News

የትምህርት ሚኒስቴር የሚያስገነባቸውን የፌዴራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

በአዲሱ የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑት በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞ በሰጡት ማብራሪያ እንዳስታወቁት በሳይንስና በቴክኖሎጂ የበቁ የነገ የዚች ሀገር መሪ መሆን የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቹ ከሁሉም አካባበዎች የሚመጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው፣ አብሮ መኖርና ማደግን የሚለምዱባቸውና የአገሪቱ የወደፊት መሪዎችን የምናፈራባቸው ቦታዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡
በዚህም መነሻ የትምህርት ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ድረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑትን በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ ከአርባ የማያንሱ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናዎች ከሞላ ጎደል ሁሉም ተማሪዎችን ማሳለፍ መቻላቸውንም በአብነት አንስተዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ በተገነቡት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል መልምሎ ለማስገባት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን ለዚህም ተማሪዎች ተገቢውን መስፈርት አሟልተው እንዲጠባበቁ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል።
በአዲሱ የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑት በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞ በሰጡት ማብራሪያ እንዳስታወቁት በሳይንስና በቴክኖሎጂ የበቁ የነገ የዚች ሀገር መሪ መሆን የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቹ ከሁሉም አካባበዎች የሚመጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው፣ አብሮ መኖርና ማደግን የሚለምዱባቸውና የአገሪቱ የወደፊት መሪዎችን የምናፈራባቸው ቦታዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡
በዚህም መነሻ የትምህርት ሚኒስቴር በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች እያስገነባቸው ካሉ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ድረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል የተወሰኑትን በመጪው የትምህርት ዘመን ስራ ለማስጀመር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በአገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ ከአርባ የማያንሱ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናዎች ከሞላ ጎደል ሁሉም ተማሪዎችን ማሳለፍ መቻላቸውንም በአብነት አንስተዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ በተገነቡት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል መልምሎ ለማስገባት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን ለዚህም ተማሪዎች ተገቢውን መስፈርት አሟልተው እንዲጠባበቁ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል።
Jul 17, 2025 757
National News

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከባለፉት ሶስት አመታት በተሻለ መልኩ በሠላም እና በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የታለመለትን ግብ በመምታት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
ሚንስትሩ የነበረውን የፈተና አሰጣጥ ሂደት አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት ሶስት አመታት በተወሰነ መልኩ ያጋጥሙ የነበሩ የጸጥታ ችግሮች፣ የፈተና ስርቆት ሙከራዎች፣ የፈተና ስርዓትና አስተዳደር የዲሲፒሊን ግድፈቶች በዘንድሮው አመት ቀንሰው መገኘታቸውን አብራርተዋል።
ለዚህም የበይነ መረብ የፈተና ሽፋን በአንድ አመት ውስጥ በአራት እጥፍ ማደጉ፤የፈተና ግብረ ሀይሉ ያልተቆጠበ ጥረት፤ እንዲሁም ተማሪዎች ሰርቶ ውጤት ማምጣት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን መገንዘባቸውና መሰል ለውጦች ችግሮች ጎልተው እንዳይስተዋሉ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ተናግረዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናው በአራት ዙሮች እንዲሠጥ የተደረገ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በአራቱም ዙሮች የተሰጡ ፈተናዎች ተቀራራቢ (አቻ) መሆናቸውን አብራርተዋል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ከተመዘገቡ ተፈታኞች 608,742 መካከል 581,905 (95.6%) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 134,828 (23.2%) በበይነ መረብ ብቻ የተፈተኑ መሆናቸው ተብራርቷል።
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በአማራ ብሔራዊ ክልል ያሉ እና የተወሰኑ የህግ ታራሚዎች በድምሩ 4,966 ተፈታኞች ከነሐሴ 26-28/2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር የተዘጋጀላቸውን ፈተና በወረቀት የሚወስዱ መሆኑንም አያይዘው አሳውቀዋል።
በ2016 የትምህርት ዘመን በበይነ መረብ የተፈተኑ ተፈታኞች ቁጥር 29,727 ብቻ የነበረ ሲሆን በዘንድሮ አመት ወደ 134,825 መድረሱ ከፍተኛ ስኬት መሆኑ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተብራርቷል።
በመጨረሻም በፈተና አሰጣጥና አስተዳደር ሂደት ውስጥ የድርሻቸውን ላበረከቱ ሁለ የትምህርት ሚኒስቴር ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ብሏል።
የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የታለመለትን ግብ በመምታት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
ሚንስትሩ የነበረውን የፈተና አሰጣጥ ሂደት አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት ሶስት አመታት በተወሰነ መልኩ ያጋጥሙ የነበሩ የጸጥታ ችግሮች፣ የፈተና ስርቆት ሙከራዎች፣ የፈተና ስርዓትና አስተዳደር የዲሲፒሊን ግድፈቶች በዘንድሮው አመት ቀንሰው መገኘታቸውን አብራርተዋል።
ለዚህም የበይነ መረብ የፈተና ሽፋን በአንድ አመት ውስጥ በአራት እጥፍ ማደጉ፤የፈተና ግብረ ሀይሉ ያልተቆጠበ ጥረት፤ እንዲሁም ተማሪዎች ሰርቶ ውጤት ማምጣት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን መገንዘባቸውና መሰል ለውጦች ችግሮች ጎልተው እንዳይስተዋሉ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ተናግረዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናው በአራት ዙሮች እንዲሠጥ የተደረገ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በአራቱም ዙሮች የተሰጡ ፈተናዎች ተቀራራቢ (አቻ) መሆናቸውን አብራርተዋል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ከተመዘገቡ ተፈታኞች 608,742 መካከል 581,905 (95.6%) ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 134,828 (23.2%) በበይነ መረብ ብቻ የተፈተኑ መሆናቸው ተብራርቷል።
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በአማራ ብሔራዊ ክልል ያሉ እና የተወሰኑ የህግ ታራሚዎች በድምሩ 4,966 ተፈታኞች ከነሐሴ 26-28/2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር የተዘጋጀላቸውን ፈተና በወረቀት የሚወስዱ መሆኑንም አያይዘው አሳውቀዋል።
በ2016 የትምህርት ዘመን በበይነ መረብ የተፈተኑ ተፈታኞች ቁጥር 29,727 ብቻ የነበረ ሲሆን በዘንድሮ አመት ወደ 134,825 መድረሱ ከፍተኛ ስኬት መሆኑ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተብራርቷል።
በመጨረሻም በፈተና አሰጣጥና አስተዳደር ሂደት ውስጥ የድርሻቸውን ላበረከቱ ሁለ የትምህርት ሚኒስቴር ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ብሏል።
Jul 16, 2025 567
National News

የ2017 ትምህርት ዘመንየ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ሀገር አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና መጠናቀቁን ተገልጿል።
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም በመላ አገሪቱ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡
ከዝግጅት ጀምሮ በፈተናው ወቅት በየደረጃው የሚገኙ በፈተናው ስራ የተሳተፉ ባለሙያዎች ፣ አመራሮችና ባለድርሻዎች በፈተናው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው ፈተናው በሰላም ተጠናቋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የፈተናው ስራ እንዲሳካ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለተወጡ ኃላፊዎች፣ አስተባባሪዎች፣ ፈታኞች፣ የጸጥታ አስከባሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻዎች ላበረከቱት አስዋጽኦ ምስጋና ያቀርባል፡፡
ተፈታኞችም ፈተናው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላሳዩት በጎ ስነ- ምግባር አያመሰገነ መልካም እድል እንዲገጥማቸው ትምህርት ሚኒስቴር ምኞቱን ይገልጻል፡፡
የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀትና በበይነ መረብ በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።

 

በአገር አቀፍ ደረጃ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና መጠናቀቁን ተገልጿል።
ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም በመላ አገሪቱ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡
ከዝግጅት ጀምሮ በፈተናው ወቅት በየደረጃው የሚገኙ በፈተናው ስራ የተሳተፉ ባለሙያዎች ፣ አመራሮችና ባለድርሻዎች በፈተናው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው ፈተናው በሰላም ተጠናቋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የፈተናው ስራ እንዲሳካ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ለተወጡ ኃላፊዎች፣ አስተባባሪዎች፣ ፈታኞች፣ የጸጥታ አስከባሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻዎች ላበረከቱት አስዋጽኦ ምስጋና ያቀርባል፡፡
ተፈታኞችም ፈተናው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላሳዩት በጎ ስነ- ምግባር አያመሰገነ መልካም እድል እንዲገጥማቸው ትምህርት ሚኒስቴር ምኞቱን ይገልጻል፡፡
የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀትና በበይነ መረብ በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።
Jul 15, 2025 588
National News

ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርቱ ዘርፍ ያላትን ትብብር አጠናክራ መቀጠል እንደምትፈልግ ተገለጸ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር Mr.Monday የተመራ የልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር የቆየ ግንኙነት በተለይም በትምህርቱ ዘርፉ ጠንካራ ትብብር እንደነበራት ጠቅሰው አሁን ኢትዮጵያ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትኩረት በመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም እርምጃዎችን አብራርተዋል።

የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር Mr.Monday በበኩላቸው ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንደነበራት አንስተው ይህንን ታሪካዊ ግንኙነት ሀገራቸው የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ከተመረቁ ተማሪዎች መካከል 200 የሚሆኑት በሀገራቸው መንግስት በተለያዩ ቦታዎች ተቀጥረው አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል የምትሰጣቸው ደቡብ ሱዳናውያንን በሚመለከት፣ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርስቲ የሚደረግ ትብብር፣ በጋራ የሚሰሩ ጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን የትምህርት ሚኒስቴር እና ለከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የአቅም ግንባታ ሥልጠናና ድጋፍ በሚደረግባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በመድረኩም በኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል ያገኙ ደቡብ ሱዳናውያን ከመኝታ፣ ከምግብ  እንዲሁም ከኢሚግሬሽን ጋር ተያይዞ ያሉ ወጪዎች በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈነው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተጠቅሷል።

በመጨረሻም ክቡር ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን ተገኝተው ጉብኝት እንዲያደርጉ የደቡብ/ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋብዘዋቸዋል።

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር የቆየ ግንኙነት በተለይም በትምህርቱ ዘርፉ ጠንካራ ትብብር እንደነበራት ጠቅሰው አሁን ኢትዮጵያ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትኩረት በመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም እርምጃዎችን አብራርተዋል።

የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር Mr.Monday በበኩላቸው ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንደነበራት አንስተው ይህንን ታሪካዊ ግንኙነት ሀገራቸው የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ከተመረቁ ተማሪዎች መካከል 200 የሚሆኑት በሀገራቸው መንግስት በተለያዩ ቦታዎች ተቀጥረው አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል የምትሰጣቸው ደቡብ ሱዳናውያንን በሚመለከት፣ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርስቲ የሚደረግ ትብብር፣ በጋራ የሚሰሩ ጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን የትምህርት ሚኒስቴር እና ለከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የአቅም ግንባታ ሥልጠናና ድጋፍ በሚደረግባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በመድረኩም በኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል ያገኙ ደቡብ ሱዳናውያን ከመኝታ፣ ከምግብ  እንዲሁም ከኢሚግሬሽን ጋር ተያይዞ ያሉ ወጪዎች በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈነው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተጠቅሷል።

በመጨረሻም ክቡር ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን ተገኝተው ጉብኝት እንዲያደርጉ የደቡብ/ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋብዘዋቸዋል።

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

Jul 11, 2025 426
National News

ማስታወቂያ

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

 

 

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ ለተማሪዎችና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን

 

 

Jul 11, 2025 1K
Recent News
Follow Us