Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

The FDRE Ministry of Education is a governmental institution headquartered in Arada Sub City, Addis Ababa, Ethiopia.

Our Recent News

Reads Our Latest News and Events

National News

በተለያዩ የትምህርት መስክ ሰልጥነው ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ አማራጭ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊገባ መሆኑ ተገለፀ። አዲስ በተዘጋጀው አማራጭ የመምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴር በመምህርነት ሙያ የሚታየውን የሥልጠና እጥረት ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሰልጥነው የሚገኙና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊያሰገባ መሆኑን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ሀገራችን የመምህርነት ሙያ ማሰልጠን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለት ቢሆንም አማራጭ ወደ መምህርነት ለመግባት ለሚፈልጉት አዲስ መንገድ መክፈት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ተጨማሪ ሥልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሥልጠና ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄድ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት የተለያዩ አማራጮች ተቀርፀው እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም መምህር ሆነው መሥራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የሚያስተምሩት ትምህርት አይነት ይዘት ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋልም ተብሏል።
የመምህራንና የትምህር አመራር ልማት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በበኩላቸው የሀገራችንን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እየተጠኑ ወደ ስራ ማስገባት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም በተደረገ የዳሰሳ ጥናት አብዛኞች በተለያዩ የትምህርት መስክ የተመረቁ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳለም ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
የሥልጠና ማዕቀፉን ወደ ሥራ ለማስገባትም ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ መምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴር በመምህርነት ሙያ የሚታየውን የሥልጠና እጥረት ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሰልጥነው የሚገኙና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊያሰገባ መሆኑን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ሀገራችን የመምህርነት ሙያ ማሰልጠን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለት ቢሆንም አማራጭ ወደ መምህርነት ለመግባት ለሚፈልጉት አዲስ መንገድ መክፈት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ተጨማሪ ሥልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሥልጠና ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄድ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት የተለያዩ አማራጮች ተቀርፀው እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም መምህር ሆነው መሥራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የሚያስተምሩት ትምህርት አይነት ይዘት ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋልም ተብሏል።
የመምህራንና የትምህር አመራር ልማት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በበኩላቸው የሀገራችንን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እየተጠኑ ወደ ስራ ማስገባት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም በተደረገ የዳሰሳ ጥናት አብዛኞች በተለያዩ የትምህርት መስክ የተመረቁ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳለም ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
የሥልጠና ማዕቀፉን ወደ ሥራ ለማስገባትም ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ መምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።
Jun 05, 2025 41
National News

ኩረጃን የሚጠየፍ ትውልድ ለመፍጠር እስካሁን በተወሰዱ እርምጃዎች በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር መቻሉ ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ያለውን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የትምህርት ምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል እንደሆነ ይታወቃል።
በዚህ ሂደት እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በማስመልከት ማብራሪያ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት እውቀት ሲሆን ሰርተፊኬት ደግሞ ያንን እውቀት የምንለካበት ነው ብለዋል።
በስርቆት፣ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እውቀት ሳይኖር ሰርተፊኬት ማግኘት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ እውቀት አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ሰርተፊኬቱ እውቀት አለህ ስለሚለው ምንም ሳያቅ ሰርተፊኬት በእጁ ስላለው ብቻ እውቀት አለኝ ብሎ የሚያምን የህብረተሰብ ክፍል ይፈጠራል፤ ይህም ህብረተሰቡን በጣም እንደሚጎዳው አብራርተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ተንሰራፍቶ የነበረውን ማጭበርበር፣ ስርቆትና ኩረጃ ተማሪዎች ብቻ የሚያደርጉት ቢሆን ኖሮ የልጆቹ ችግር ነው ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። ነገር ግን ይህን የሚያደርጉት ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤት አስተዳደሮች፣ የክልል ባለ ስልጠናት እና ሌሎችም የኛ አካባቢ ልጆች እንዲያልፉ በሚል የሚያደርጉት በመሆኑ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ የተገባበት እንደነበር አንስተዋል።
በመሆኑም ወደፊት ትውልዱን በጥራት ማስተማር አለብን ካልን ከመሰረቱ ችግሩን መፍታትና በኩረጃና በማጭበርበር የሚገኝ እውቀት እንደሌለና ይህም ሀገር እንደሚጎዳ በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም ይህንን ስብራት ለማስተካከል በተወሰደው የለውጥ እርምጃ ተማሪዎች በትምህርት ዘርፉ በቀላሉ አጭበርብሮና ኮርጆ ማለፍ የለም የሚለውን በማወቅ በሥርዓቱ ማጥናት፣ ቤተ መጽሃፍት መግባት፣ ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም፣ በትርፍ ጊዜያቸው ቲቶሪያል መማርና ለትምህርታቸው በቂ ትኩረት መስጠት ጀምረዋል።
መምህራንም በአግባቡ ተዘጋጅተው ማስተማርና ተማሪዎችን በሚገባ ማዘጋጀት፣ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራንም ሁሉም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተከታትለው ከክፍል ክፍል በትክክል ተመዝነው እንዲያልፉ ማድረግ የጀመሩበት፣
በየክልሉ ያለው የትምህርት መዋቅርም በኩረጃ የኔ አካባቢ ይህን ያህል አለፈ ከሚል የቁጥር ጨዋታ ወጥተው በትክክል የትምህርት ምዘና በየደረጃው በማድረግ ልጆች ባላቸው እውቀት ብቻ ተመዝነው የሚያልፉበት ሥርዓት እየፈጠሩ ይገኛል። ለአብነትም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በአግባቡ እየተገበሩ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም ይህንን ማስቀጠል ከተቻለ የምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን በሚገባ ያስተካክለዋል። የገጠመውን የሞራል ክስረት በሚገባ አስወግዶ ትምህርት በእውቀትና በችሎታ ብቻ የሚለው በጀመርነው አግባብ ወደ ኋላ ሳይመለው ማስረጽ ከቻልን ለምናደርገው የትምህርት ጥራት መሻሻል እንደ መነሻ ይሆናልም ብለዋል።
በአጠቃላይ የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል ከተጀመረ ጀምሮ በተወሰዱ እርምጃዎች ከአሁን በኋላ በሁሉም ዘንድ ግልጽ በሆነ መንገድ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እንደሌለ እና ተምሮና ተግቶ በማጥናት ብቻ ውጤት እንደሚገኝ በተማሪዎችና በማህበረሰቡ ዘንድ መተማመን መፈጠሩንም ገልጸዋል።
አክለውም ዘንድሮም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን በተለመደው አግባብ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉ ጠቅሰው በተለይም ከባለፈው ዓመት በተሻለ 150 ሺ የሚደርሱ ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በዚህ ሂደት በቀጣይ ሶስት ዓመታት ሁሉም ተማሪዎች በበየነ መረብ የሚፈተኑበት ሁኔታ ይፈጠራል ያሉት ሚኒስትሩ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ በዚህ መልኩ መስመር ከያዘ ብቃት ያላቸውና ተወዳድሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት ሌሎች የትምህርት ጥራት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ተግባራት ላይም ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች በወረቀትና በበየነ መረብ ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ያለውን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የትምህርት ምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል እንደሆነ ይታወቃል።
በዚህ ሂደት እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በማስመልከት ማብራሪያ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት እውቀት ሲሆን ሰርተፊኬት ደግሞ ያንን እውቀት የምንለካበት ነው ብለዋል።
በስርቆት፣ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እውቀት ሳይኖር ሰርተፊኬት ማግኘት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ እውቀት አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ሰርተፊኬቱ እውቀት አለህ ስለሚለው ምንም ሳያቅ ሰርተፊኬት በእጁ ስላለው ብቻ እውቀት አለኝ ብሎ የሚያምን የህብረተሰብ ክፍል ይፈጠራል፤ ይህም ህብረተሰቡን በጣም እንደሚጎዳው አብራርተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ተንሰራፍቶ የነበረውን ማጭበርበር፣ ስርቆትና ኩረጃ ተማሪዎች ብቻ የሚያደርጉት ቢሆን ኖሮ የልጆቹ ችግር ነው ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። ነገር ግን ይህን የሚያደርጉት ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤት አስተዳደሮች፣ የክልል ባለ ስልጠናት እና ሌሎችም የኛ አካባቢ ልጆች እንዲያልፉ በሚል የሚያደርጉት በመሆኑ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ የተገባበት እንደነበር አንስተዋል።
በመሆኑም ወደፊት ትውልዱን በጥራት ማስተማር አለብን ካልን ከመሰረቱ ችግሩን መፍታትና በኩረጃና በማጭበርበር የሚገኝ እውቀት እንደሌለና ይህም ሀገር እንደሚጎዳ በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም ይህንን ስብራት ለማስተካከል በተወሰደው የለውጥ እርምጃ ተማሪዎች በትምህርት ዘርፉ በቀላሉ አጭበርብሮና ኮርጆ ማለፍ የለም የሚለውን በማወቅ በሥርዓቱ ማጥናት፣ ቤተ መጽሃፍት መግባት፣ ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም፣ በትርፍ ጊዜያቸው ቲቶሪያል መማርና ለትምህርታቸው በቂ ትኩረት መስጠት ጀምረዋል።
መምህራንም በአግባቡ ተዘጋጅተው ማስተማርና ተማሪዎችን በሚገባ ማዘጋጀት፣ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራንም ሁሉም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተከታትለው ከክፍል ክፍል በትክክል ተመዝነው እንዲያልፉ ማድረግ የጀመሩበት፣
በየክልሉ ያለው የትምህርት መዋቅርም በኩረጃ የኔ አካባቢ ይህን ያህል አለፈ ከሚል የቁጥር ጨዋታ ወጥተው በትክክል የትምህርት ምዘና በየደረጃው በማድረግ ልጆች ባላቸው እውቀት ብቻ ተመዝነው የሚያልፉበት ሥርዓት እየፈጠሩ ይገኛል። ለአብነትም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በአግባቡ እየተገበሩ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም ይህንን ማስቀጠል ከተቻለ የምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን በሚገባ ያስተካክለዋል። የገጠመውን የሞራል ክስረት በሚገባ አስወግዶ ትምህርት በእውቀትና በችሎታ ብቻ የሚለው በጀመርነው አግባብ ወደ ኋላ ሳይመለው ማስረጽ ከቻልን ለምናደርገው የትምህርት ጥራት መሻሻል እንደ መነሻ ይሆናልም ብለዋል።
በአጠቃላይ የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል ከተጀመረ ጀምሮ በተወሰዱ እርምጃዎች ከአሁን በኋላ በሁሉም ዘንድ ግልጽ በሆነ መንገድ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እንደሌለ እና ተምሮና ተግቶ በማጥናት ብቻ ውጤት እንደሚገኝ በተማሪዎችና በማህበረሰቡ ዘንድ መተማመን መፈጠሩንም ገልጸዋል።
አክለውም ዘንድሮም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን በተለመደው አግባብ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉ ጠቅሰው በተለይም ከባለፈው ዓመት በተሻለ 150 ሺ የሚደርሱ ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በዚህ ሂደት በቀጣይ ሶስት ዓመታት ሁሉም ተማሪዎች በበየነ መረብ የሚፈተኑበት ሁኔታ ይፈጠራል ያሉት ሚኒስትሩ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ በዚህ መልኩ መስመር ከያዘ ብቃት ያላቸውና ተወዳድሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት ሌሎች የትምህርት ጥራት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ተግባራት ላይም ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች በወረቀትና በበየነ መረብ ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Jun 03, 2025 372
National News

ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰራ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በጋምቤላ ክልል በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በየአካባቢው መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በጋምቤላ ክልል የሚስተዋለውን ከፍተኛ የትምህርት ጥራት ችግርና የመማሪያ ክፍል ጥበት ለመቅረፍ የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ መጀመር አስተዋጸኦ የጎላ ይሆናል ብለዋል።
አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ግዴታ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሰፊ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም በመላ ሀገሪቱ 31 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 15ቱ በትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም 16ቱ ደግሞ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት እንደሚገነቡ አንስተው በተለይም በቂ የመሰረተ ልማት ባልተሟላላቸው ክልሎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው ይህ ትምህርት ቤት በክልሉ የትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው በክልላችን የተመዘገበውን ዝቅተኛ የተማሪ ውጤት ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።
የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ፈተናዎች ማለፍ የሚቻለው ዘመኑ የሚጠይቀውን ክህሎት የተላበሱ፣ ችግር ፈቺ ፣ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት ሲቻል መሆኑን አንስው፤
የትምህርት ጥራት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በክልሉ የትምህርት ጥራት እንዲሻሻል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የዚህ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሙሉ ወጪ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፈን የተገለፀ ሲሆን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
በዚህም ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ክትትል ለማድረግ በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የሥምምነት ፊርማ ተከናውኗል።
በጋምቤላ ክልል በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በየአካባቢው መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በጋምቤላ ክልል የሚስተዋለውን ከፍተኛ የትምህርት ጥራት ችግርና የመማሪያ ክፍል ጥበት ለመቅረፍ የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ መጀመር አስተዋጸኦ የጎላ ይሆናል ብለዋል።
አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ግዴታ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሰፊ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም በመላ ሀገሪቱ 31 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 15ቱ በትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም 16ቱ ደግሞ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት እንደሚገነቡ አንስተው በተለይም በቂ የመሰረተ ልማት ባልተሟላላቸው ክልሎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው ይህ ትምህርት ቤት በክልሉ የትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው በክልላችን የተመዘገበውን ዝቅተኛ የተማሪ ውጤት ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።
የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ፈተናዎች ማለፍ የሚቻለው ዘመኑ የሚጠይቀውን ክህሎት የተላበሱ፣ ችግር ፈቺ ፣ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት ሲቻል መሆኑን አንስው፤
የትምህርት ጥራት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በክልሉ የትምህርት ጥራት እንዲሻሻል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የዚህ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሙሉ ወጪ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፈን የተገለፀ ሲሆን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
በዚህም ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ክትትል ለማድረግ በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የሥምምነት ፊርማ ተከናውኗል።
May 30, 2025 198
National News

ለትምህርት ቤቶች ግንባታ መሠረት ድጋይ አስቀምጦ መጥፋት ሳይሆን ቀጥታ ግንባታ በማስጀመር በአጭር ጊዜ አጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምሩ የሚያስችል ስልት ተቀይሶ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስቴር በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ የሚያስገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በጋራ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት ለትምህርት ቤቶች ግንባታ የመሰረት ድጋይ አስቀምጦ መጥፋት ሳይሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራን በማጠናቀቅ ግንባታዎችን በማስጀመር በተግባር በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
አክለውም ይህ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ትምህርት ቤትም መሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን መሆኑን በመግለፅ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራል ብለዋል።
ሁሉም በሀገራችን የሚኖሩ ልጆች በተቻለ መጠን ተመጣጣኝ ትምህርት፣ እውቀትና ክህሎት ማግኘት አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ አሁን ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በፍተሃዊነትና በጥራት ለማድረስ የተጀመረው ሥራ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ምቹ አካባቢን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ ትምህርት ሚኒስቴር ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየሠራቸው ያሉ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በተለይም በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ እንደ ሀገር በርካታ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም በክልሉ ያለውን ክፍተት በመለየትና ልዩ ትኩረት በመስጠት ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ግንባታው እስኪጠናቀቅ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ የሚያስገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በጋራ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት ለትምህርት ቤቶች ግንባታ የመሰረት ድጋይ አስቀምጦ መጥፋት ሳይሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራን በማጠናቀቅ ግንባታዎችን በማስጀመር በተግባር በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
አክለውም ይህ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ትምህርት ቤትም መሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን መሆኑን በመግለፅ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራል ብለዋል።
ሁሉም በሀገራችን የሚኖሩ ልጆች በተቻለ መጠን ተመጣጣኝ ትምህርት፣ እውቀትና ክህሎት ማግኘት አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ አሁን ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በፍተሃዊነትና በጥራት ለማድረስ የተጀመረው ሥራ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ምቹ አካባቢን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ ትምህርት ሚኒስቴር ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየሠራቸው ያሉ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በተለይም በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ እንደ ሀገር በርካታ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም በክልሉ ያለውን ክፍተት በመለየትና ልዩ ትኩረት በመስጠት ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ግንባታው እስኪጠናቀቅ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል።
May 30, 2025 181
National News

የአፍሪካውያ ችግር በአፍሪካውያን መፍታት እንደሚገባ ተጠቆመ፤ በኢትዮጵያ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ2025 የኢራስመስ ጉባኤ ተጠናቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በጉባዔው ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የአፍሪካ አገራትን ትብብር በማጠናከር የአፍሪካውያውያን ችግሮችን በአፍሪካውያን መፍታት ይገባል ብለዋል።
አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን ለመፍታት በትብብርና በቅንጅት አጽንኦት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመንግስት የሚመደበውን በጀት ከመጠቀም ባሻገር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ተልዕኳቸውን ማሳካት እንዳለባቸውና በኢራስመስ ፕሮግራምንና የመሳሰሉ ፕሮጀክቶችን በመጠቀም ለሀገር ልማትና ብልጽግና መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር አቶ ኮራ ጨምረው አስገንዝበዋል፡፡
በብራሰልስ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት፣ ስልጠና፣ ባህልና ሳይንስ ዳይሬክተር ጄኔራል ክሌር ሄርማን የኢራስመስ ፕሮጀክት ለአፍሪካውያን እጅግ በጣም ጠቃሚ መሆኑንና አፍሪካውያን ፕሮግራሙን በአግባቡ በማስተዋወቅና በማስፋት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባዔ እጅግ በጣም ጠቃሚ እንደነበርና ብዙ ትምህርት የተገኘበት መሆኑን አንስተው በአግባቡ በመጠቀም እንደ ሀገር የተለዩ የሪፎርም ስራዎችን ማሳካት እንደሚገባና እንደ አፍሪካ በትብብር ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተካሄደው በዘንድሮው የኢራስመስ 2025 ጉባኤ ከሰሃራ በታች የሚገኙ 32 የአፍሪካ አገራትን ጨምሮ ከ46 አገራት የተወከሉ ጉባኤተኞቾ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በጉባዔው ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የአፍሪካ አገራትን ትብብር በማጠናከር የአፍሪካውያውያን ችግሮችን በአፍሪካውያን መፍታት ይገባል ብለዋል።
አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን ለመፍታት በትብብርና በቅንጅት አጽንኦት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመንግስት የሚመደበውን በጀት ከመጠቀም ባሻገር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ተልዕኳቸውን ማሳካት እንዳለባቸውና በኢራስመስ ፕሮግራምንና የመሳሰሉ ፕሮጀክቶችን በመጠቀም ለሀገር ልማትና ብልጽግና መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር አቶ ኮራ ጨምረው አስገንዝበዋል፡፡
በብራሰልስ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት፣ ስልጠና፣ ባህልና ሳይንስ ዳይሬክተር ጄኔራል ክሌር ሄርማን የኢራስመስ ፕሮጀክት ለአፍሪካውያን እጅግ በጣም ጠቃሚ መሆኑንና አፍሪካውያን ፕሮግራሙን በአግባቡ በማስተዋወቅና በማስፋት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባዔ እጅግ በጣም ጠቃሚ እንደነበርና ብዙ ትምህርት የተገኘበት መሆኑን አንስተው በአግባቡ በመጠቀም እንደ ሀገር የተለዩ የሪፎርም ስራዎችን ማሳካት እንደሚገባና እንደ አፍሪካ በትብብር ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተካሄደው በዘንድሮው የኢራስመስ 2025 ጉባኤ ከሰሃራ በታች የሚገኙ 32 የአፍሪካ አገራትን ጨምሮ ከ46 አገራት የተወከሉ ጉባኤተኞቾ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
May 23, 2025 379
National News

የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን በለንደን እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2025 ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልኡካን ቡድን በለንደን እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2025 ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ እየተካሄደ ካለው የትምህርት ፎረሙ ጎን ለጎን ከእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትር ባሮነስ ቻፕማን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በዚህም ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም የገልጹላቸው ሲሆን በራስ አቅም በ “ትምህርት ለትውልድ’’ ህዝባዊ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻን በተመለከተ ስለተገኘው ውጤት አብራርተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ከሥርዓተ ትምህርት፣ ከመምህራንና የትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና እና ከእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጋር በተያያዘ የተጀመሩ ሥራዎችን ጠቅሰው፣
እነዚህ በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ ሪፎርሞች በፍጥነት እንዲሳኩ የልማት አጋሮችና በተለይም የእንግሊዝ መንግስት ድጋፉን እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትሯ ባሮነስ ቻፕማን በበኩላቸው በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደርጉትን ጉብኝት በማስታወስ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ለውጥ አድንቀዋል፣
የተጀመረውን የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ምንም እንኳን በእንግሊዝ መንግስት የተደረገው የበጀት ቅነሳ (budget cuts) ቢኖርም በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚካሄደውን ሪፎርም ለመደገፍ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ክቡር ሚኒስትሩ ከተለያዩ አገራት የትምህርት ሚንስትሮች ጋር በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በተመለከተ ውይይቶች አድርገዋል።
በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎርም ላይ ከ150 በላይ የትምህርት ሚኒስትሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን እየተሳተፈ እንደሚገኝም የተገለጸ ሲሆን፣
ክቡር ሚኒስትሩም በዓለም አቀፉ የትምህርት ፎረም ላይ ‘’ የገንዘብ ድጋፍን ማሻሻል፣ ውጤታማ እቅድ በማውጣትና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመለየት ረገድ አንዳችን ከሌላችን ምን እንማራለን?’’ በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የመነሻ ፅሁፍ አቅርበዋል።
በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልኡካን ቡድን በለንደን እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2025 ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ እየተካሄደ ካለው የትምህርት ፎረሙ ጎን ለጎን ከእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትር ባሮነስ ቻፕማን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በዚህም ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም የገልጹላቸው ሲሆን በራስ አቅም በ “ትምህርት ለትውልድ’’ ህዝባዊ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻን በተመለከተ ስለተገኘው ውጤት አብራርተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ከሥርዓተ ትምህርት፣ ከመምህራንና የትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና እና ከእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጋር በተያያዘ የተጀመሩ ሥራዎችን ጠቅሰው፣
እነዚህ በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ ሪፎርሞች በፍጥነት እንዲሳኩ የልማት አጋሮችና በተለይም የእንግሊዝ መንግስት ድጋፉን እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትሯ ባሮነስ ቻፕማን በበኩላቸው በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደርጉትን ጉብኝት በማስታወስ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ለውጥ አድንቀዋል፣
የተጀመረውን የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ምንም እንኳን በእንግሊዝ መንግስት የተደረገው የበጀት ቅነሳ (budget cuts) ቢኖርም በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚካሄደውን ሪፎርም ለመደገፍ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ክቡር ሚኒስትሩ ከተለያዩ አገራት የትምህርት ሚንስትሮች ጋር በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በተመለከተ ውይይቶች አድርገዋል።
በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎርም ላይ ከ150 በላይ የትምህርት ሚኒስትሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን እየተሳተፈ እንደሚገኝም የተገለጸ ሲሆን፣
ክቡር ሚኒስትሩም በዓለም አቀፉ የትምህርት ፎረም ላይ ‘’ የገንዘብ ድጋፍን ማሻሻል፣ ውጤታማ እቅድ በማውጣትና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመለየት ረገድ አንዳችን ከሌላችን ምን እንማራለን?’’ በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የመነሻ ፅሁፍ አቅርበዋል።
May 22, 2025 314

Our Ministers

MINISTER

H.E Pro. Birhanu Nega

Ministry of Education

STATE MINISTER

H.E Mrs. Ayelech Eshete

General Education

STATE MINISTER

H.E Ato Kora Tushune

Higher Education

Organization structure

This is The Main Ministry Organization Structure Chart

General Education

Curriculum Development Executive

Head, Language and Co-curricular Education Curriculum Desk

Head, Social Science Education Curriculum Desk

Head, Natural Science Education Curriculum Desk

Head, Career and Technical Education Curriculum Desk

Teachers’ and Educational Leaders’ Development Executive

Head, Teachers’ and Educational Leaders Development Desk

Head, Education Language Development Desk

Head, STEAM DESK

Educational Program and Quality Improvement Executive

Head, Education Programs and Quality Improvement Desk

Head, Pastoralist and Special Needs Education Desk

Head, Education Infrastructure and Service Desk

Head, General Education Inspection Desk

Adult and Non-formal Education Programs Executive

Head, Adults’ Basic Education Desk

Head, Non-Formal and Lifelong Education Programs Desk

Higher Education

Academic Affairs Executive

Head, Competency and Quality Improvement Desk

Head, Curriculum and Programs Desk

Head, Teachers’ and Students’ Development Desk

Head, Private Higher Education Institutions Service Desk

Research and Community Engagement Executive

Head, Research and Extension Desk

Head, Research Ethics Desk

Head, Institutional Linkage and Technology Transfer Desk

Head, Community Engagement and Indigenous Knowledge Desk

Governance and Infrastructure Executive

Head, Administration Affairs Desk

Head, Institutional Structure and Leadership Desk

Head, Infrastructure and Input Desk

Head, Scholarship and Internationalization Desk

ICT and Digital Education Executive

Head, Education Multimedia Program Development Desk

Head, School Net ICT Desk

Head, Education Media Studio Operation and Administration Desk

Head, Network Technical Desk

Head, Network Operation Desk