Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

The FDRE Ministry of Education is a governmental institution headquartered in Arada Sub City, Addis Ababa, Ethiopia.

Our Recent News

Reads Our Latest News and Events

National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ከደቡብ አፍሪካ የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይትም University of South Africa (UNISA) በኢትዮጵያ እንዴት በትብብር መስራት እንደሚችል ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
Nov 29, 2025 53
National News

እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስ በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
Nov 23, 2025 42
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በሲንጋፖር አምባሳደር የተመራ የልዑካን ቡድንን ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
Nov 22, 2025 37
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ የናይጄሪያ ቴክኒካል ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከናይጄሪያ ቴክኒክ ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑክ ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያይተዋል።

የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።
በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።
ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።
‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።

በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።

ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።

‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
Nov 21, 2025 343
National News

34ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተጀመረ፤

'ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል በተጀመረው ጉባዔ የ2017 የትምህርት ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ይገመገማል።
‎ጉባዌው በ2018 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ለተሻለ አፈጻጸም የሚያግዙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ጉባዔ የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
‎በተጨማሪም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፣የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፣የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶችና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
'ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል በተጀመረው ጉባዔ የ2017 የትምህርት ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ይገመገማል።
‎ጉባዌው በ2018 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ለተሻለ አፈጻጸም የሚያግዙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ጉባዔ የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
‎በተጨማሪም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፣የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፣የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶችና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
Nov 11, 2025 476
National News

ትውልድን የመገንባት መንገዳችን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ስለሆነ ዘርፉን የሚያሻግሩ አማራጮችን ማስፋት እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አሳሰቡ፤

ትውልድን የመገንባት መንገዳችን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ስለሆነ ዘርፉን የሚያሻግሩ አማራጮችን ማስፋት እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አሳስበዋል።
በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የለውጥ ተግባራት ተነድፈው እየተተገበሩ መሆኑት የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ባለፈው የትምህርት ዘመን ጸድቆ ወደትግብራ የገባውን የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ በሚገባ መተግበር ይገባል ብለዋል።
አያይዘውም ለተማሪዎች ውጤታማነት የትምህርት ቤት ምገባ፣ የመምህራንና የት/ቤት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና በትኩረት እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዚህ ዓመትም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሰገንዝበዋል።
በተጨማሪም የመምህራን የጥቅማጥቅምና መሠል ጥያቄዎችን ለመመለስ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች የእቅዳቸው አካል አርጎ ከመስራት ባለፈ በአካባቢ ያለን ሀብት አሟጦ በመጠቀም ለሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መልስ መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ለተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም የክልልና የከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ተጠያቂነትን በማረጋገጥ በሀላፊነት መንፈስ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ትውልድን የመገንባት መንገዳችን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ስለሆነ ዘርፉን የሚያሻግሩ አማራጮችን ማስፋት እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አሳስበዋል።
በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የለውጥ ተግባራት ተነድፈው እየተተገበሩ መሆኑት የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ባለፈው የትምህርት ዘመን ጸድቆ ወደትግብራ የገባውን የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ በሚገባ መተግበር ይገባል ብለዋል።
አያይዘውም ለተማሪዎች ውጤታማነት የትምህርት ቤት ምገባ፣ የመምህራንና የት/ቤት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና በትኩረት እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዚህ ዓመትም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሰገንዝበዋል።
በተጨማሪም የመምህራን የጥቅማጥቅምና መሠል ጥያቄዎችን ለመመለስ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች የእቅዳቸው አካል አርጎ ከመስራት ባለፈ በአካባቢ ያለን ሀብት አሟጦ በመጠቀም ለሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መልስ መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ለተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም የክልልና የከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ተጠያቂነትን በማረጋገጥ በሀላፊነት መንፈስ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
Nov 11, 2025 446

Our Ministers

MINISTER

H.E Professor. Birhanu Nega

Ministry of Education

STATE MINISTER

H.E Mrs. Ayelech Eshete

General Education

STATE MINISTER

H.E Ato Kora Tushune

Higher Education

STATE MINISTER

Professor Kindeya Gebrehiwot

Advisor to the Ministry of Education

Organization structure

This is The Main Ministry Organization Structure Chart

General Education

Curriculum Development Executive

Head, Language and Co-curricular Education Curriculum Desk

Head, Social Science Education Curriculum Desk

Head, Natural Science Education Curriculum Desk

Head, Career and Technical Education Curriculum Desk

Teachers’ and Educational Leaders’ Development Executive

Head, Teachers’ and Educational Leaders Development Desk

Head, Education Language Development Desk

Head, STEAM DESK

Educational Program and Quality Improvement Executive

Head, Education Programs and Quality Improvement Desk

Head, Pastoralist and Special Needs Education Desk

Head, Education Infrastructure and Service Desk

Head, General Education Inspection Desk

Adult and Non-formal Education Programs Executive

Head, Adults’ Basic Education Desk

Head, Non-Formal and Lifelong Education Programs Desk

Higher Education

Academic Affairs Executive

Head, Competency and Quality Improvement Desk

Head, Curriculum and Programs Desk

Head, Teachers’ and Students’ Development Desk

Head, Private Higher Education Institutions Service Desk

Research and Community Engagement Executive

Head, Research and Extension Desk

Head, Research Ethics Desk

Head, Institutional Linkage and Technology Transfer Desk

Head, Community Engagement and Indigenous Knowledge Desk

Governance and Infrastructure Executive

Head, Administration Affairs Desk

Head, Institutional Structure and Leadership Desk

Head, Infrastructure and Input Desk

Head, Scholarship and Internationalization Desk

ICT and Digital Education Executive

Head, Education Multimedia Program Development Desk

Head, School Net ICT Desk

Head, Education Media Studio Operation and Administration Desk

Head, Network Technical Desk

Head, Network Operation Desk