እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ዙሪያ በምንም መልኩ በድሃና በሀብታም መካከል ልዩነት እንዳይኖር በሁሉም አካባቢዎች ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች እየተሰሩ መሆኑ ተገለፀ ። በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የተገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የሳውላ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በህ/ተ/ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ ቤልጅጌ(ዶ/ር) እና የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደ ሀገር በትምህርት ዙሪያ በድሃና ሀብታም መካከል በምንም መልኩ ልዩነት መኖር የለበትም በሚል የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ዜጎች ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም ተማሪዎች ትምህርት ቤቶቻቸውን ወደውና ፈልገው እንዲመጡ የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል በትምህርት ለትውልድ ህዝባዊ ንቅናቄ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
እንደ ሀገር በአዲሱ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ዲዛይን መሠረት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰው ይህ ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም እንደ ከዚህ ቀደሙ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉት ሚኒስትሩ በገባነው ቃል መሠረት በአጭር ጊዜ ግንባታው ተጠናቆ ተመርቋል፤ ይህም ትምህርት ላይ የሚሰራው ሥራ ከፖለቲካ በፀዳ መልኩ በጋራ የምንሰራው ሥራ ነውም ብለዋል።
በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) በበኩላቸው የተሳካ የሀገረ መንግስት ግንባታ ከትውልድ ግንባታ ተለይቶ የሚታይ አይደለም፤ በዚህም ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑና በቴክኖሎጂ የታነፁ ዜጎችን ለማፍራት መንግስት ከታች ጀምሮ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው የሀገራችን የትምህርት ሥርዓት የገጠመው ስብራት ለውጥ ያስፈልገዋል በሚል ትምህርት ሚኒስቴር እየወሰዳቸው ባለው እርምጃ የተመዘገቡ ለውጦች እውቅና የሚሰጣቸው መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ከምንም በላይ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻልና ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች በሁሉም አካባቢዎች እንዲኖሩ እየተሰራ ያለው ሥራ የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት በትምህርት ሚኒስቴር ዲዛይን መሠረት በጥራትና ፍጥነት የተገነባ በመሆኑ ሌሎች በክልሉ ለሚገነቡ ትምህርት ቤቶችም ሞዴል ሆኖ እንደሚያገለግል ተናግረዋል ።
በመድረኩም ትምህርት ቤቱ ለተማሪዎች ምቹ ሆኖ እንዲቀጥልና አስፈላጊው መሠረተ ልማት እንዲሟላለት የዞኑና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የሳውላ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በህ/ተ/ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ ቤልጅጌ(ዶ/ር) እና የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደ ሀገር በትምህርት ዙሪያ በድሃና ሀብታም መካከል በምንም መልኩ ልዩነት መኖር የለበትም በሚል የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ዜጎች ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም ተማሪዎች ትምህርት ቤቶቻቸውን ወደውና ፈልገው እንዲመጡ የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል በትምህርት ለትውልድ ህዝባዊ ንቅናቄ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
እንደ ሀገር በአዲሱ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ዲዛይን መሠረት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰው ይህ ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም እንደ ከዚህ ቀደሙ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉት ሚኒስትሩ በገባነው ቃል መሠረት በአጭር ጊዜ ግንባታው ተጠናቆ ተመርቋል፤ ይህም ትምህርት ላይ የሚሰራው ሥራ ከፖለቲካ በፀዳ መልኩ በጋራ የምንሰራው ሥራ ነውም ብለዋል።
በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) በበኩላቸው የተሳካ የሀገረ መንግስት ግንባታ ከትውልድ ግንባታ ተለይቶ የሚታይ አይደለም፤ በዚህም ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑና በቴክኖሎጂ የታነፁ ዜጎችን ለማፍራት መንግስት ከታች ጀምሮ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው የሀገራችን የትምህርት ሥርዓት የገጠመው ስብራት ለውጥ ያስፈልገዋል በሚል ትምህርት ሚኒስቴር እየወሰዳቸው ባለው እርምጃ የተመዘገቡ ለውጦች እውቅና የሚሰጣቸው መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ከምንም በላይ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻልና ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች በሁሉም አካባቢዎች እንዲኖሩ እየተሰራ ያለው ሥራ የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት በትምህርት ሚኒስቴር ዲዛይን መሠረት በጥራትና ፍጥነት የተገነባ በመሆኑ ሌሎች በክልሉ ለሚገነቡ ትምህርት ቤቶችም ሞዴል ሆኖ እንደሚያገለግል ተናግረዋል ።
በመድረኩም ትምህርት ቤቱ ለተማሪዎች ምቹ ሆኖ እንዲቀጥልና አስፈላጊው መሠረተ ልማት እንዲሟላለት የዞኑና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
Jan 17, 2026 211
የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በክብርት ቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በተገነባ የት/ቤት ምርቃት ላይ ተገኝተው ያስተላለፉት መልዕክት

በክብርት ቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በሱርማ ወረዳ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባ ትምህርት ቤት ርክክብ ሥነሥርዓት ላይ ስንገኝ በአካባቢው የትምህርት መስክ እድገት ረገድ ዐቢይ ተግባር በመሆኑ ደስታ ይሰማናል።
ትምህርት ቤቱ በቀዳሚነት ከአካባቢው ለሚመጡ ተማሪዎች የአዳሪ ትምህርት ቤት በመሆን ያገለግላል።
ግቢው ማደሪያ ክፍሎችን፣ መማሪያ ክፍሎችን፣ በፀሃይ ኃይል የሚሰሩ በቂ ኮምፒውተሮች ያሉት የኮምፒውተር ላብራቶሪ፣ የንፁህ ውሃ ጉድጓድ፣ የተሟላ የምግብ ማብሰያ ክፍል፣ ቤተ መፃሕፍት እና የአስተዳደር ሕንፃን አካትቶ የተገነባ ነው።
ይኽ ምሉዕነት ያለው የትምህርት ከባቢ የተማሪዎችን አካዳሚያዊ ልህቀት እና ደኅንነት ለማረጋገጥ ታስቦበት የተሰራ፣ ለወጣት ተማሪ ልጆቻችን ሁሉን አቀፍ እድገት አዲስ እድል የፈጠረ ተቋም ነው።
በክብርት ቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በሱርማ ወረዳ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባ ትምህርት ቤት ርክክብ ሥነሥርዓት ላይ ስንገኝ በአካባቢው የትምህርት መስክ እድገት ረገድ ዐቢይ ተግባር በመሆኑ ደስታ ይሰማናል።
ትምህርት ቤቱ በቀዳሚነት ከአካባቢው ለሚመጡ ተማሪዎች የአዳሪ ትምህርት ቤት በመሆን ያገለግላል።
ግቢው ማደሪያ ክፍሎችን፣ መማሪያ ክፍሎችን፣ በፀሃይ ኃይል የሚሰሩ በቂ ኮምፒውተሮች ያሉት የኮምፒውተር ላብራቶሪ፣ የንፁህ ውሃ ጉድጓድ፣ የተሟላ የምግብ ማብሰያ ክፍል፣ ቤተ መፃሕፍት እና የአስተዳደር ሕንፃን አካትቶ የተገነባ ነው።
ይኽ ምሉዕነት ያለው የትምህርት ከባቢ የተማሪዎችን አካዳሚያዊ ልህቀት እና ደኅንነት ለማረጋገጥ ታስቦበት የተሰራ፣ ለወጣት ተማሪ ልጆቻችን ሁሉን አቀፍ እድገት አዲስ እድል የፈጠረ ተቋም ነው።
Jan 17, 2026 188
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በጂግጂጋ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላለፉ።

የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸው የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የጂግጂጋ የፌዴራል አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚንስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለአጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ መርሃ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም መንግስት የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታዋ በዚህ የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኛችሁ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ታሪካዊ በሆነው መርሃ ግብር የመጀመሪያዎቹ ተዋንያን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አያይዘውም ተማሪዎች ዓላማቸው ላይ ትኩረት በማድረግ በትምህርታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም ምሳሌ የሚሆኑ ዜጎች እንዲሆኑ፤ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እንደ ቤተሰብ ሆነው በታላቅ ሃላፊነት ተማሪዎችን በማገዝ ብቁ ዜጎችን እንዲያፈሩ አደራ ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር በማያያዝም እስካሁን በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድና ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ ስራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ በማስቀጠል ክፍተቶች እየተሞሉ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሄድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ መሃመድ አደን እና የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ፔሬዘዳንት ዶ/ር ሠይድ መሃመድ በመገኘት ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸው የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የጂግጂጋ የፌዴራል አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚንስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለአጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ መርሃ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም መንግስት የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታዋ በዚህ የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኛችሁ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ታሪካዊ በሆነው መርሃ ግብር የመጀመሪያዎቹ ተዋንያን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አያይዘውም ተማሪዎች ዓላማቸው ላይ ትኩረት በማድረግ በትምህርታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም ምሳሌ የሚሆኑ ዜጎች እንዲሆኑ፤ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እንደ ቤተሰብ ሆነው በታላቅ ሃላፊነት ተማሪዎችን በማገዝ ብቁ ዜጎችን እንዲያፈሩ አደራ ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር በማያያዝም እስካሁን በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድና ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ ስራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ በማስቀጠል ክፍተቶች እየተሞሉ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሄድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ መሃመድ አደን እና የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ፔሬዘዳንት ዶ/ር ሠይድ መሃመድ በመገኘት ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Dec 27, 2025 458
የሀገር ውስጥ ዜና

የዩኒቨርስቲ የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥን አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤

የጅማ ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ጌንት የ25 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥናቸው አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል።
‎የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች እንደሀገር እሰከ 80 በመቶ የሚደርስ የክሊኒካል አገልግሎት ጫና እንዳለባቸው የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታትም አየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለዩኒቨርስቲው ህክምና ማዕከል የተደረገው የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የጅማ ዩኒቨርስቲን ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የጅማ ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ጌንት የ25 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥናቸው አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል።
‎የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች እንደሀገር እሰከ 80 በመቶ የሚደርስ የክሊኒካል አገልግሎት ጫና እንዳለባቸው የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታትም አየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለዩኒቨርስቲው ህክምና ማዕከል የተደረገው የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የጅማ ዩኒቨርስቲን ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
Dec 27, 2025 401
የሀገር ውስጥ ዜና

ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የወደፊቱ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ሰብዕና የሚገነባባቸው ተቋማት መሆናቸው ተመላከተ፤ የቦንጋ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በአዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት አዳሪ ትምህርት ቤቶች የነገዎቹ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነባባቸው ቦታዎች ናቸው።
‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርት ከማቅረብ ጎን ለጎን በጥሩ ባህሪ የተገነቡ ፣ሥነምግባር የተላበሱና በሙያቸው የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸውንም ክቡር አቶ ኮራ አስገንዝበዋል።
‎የትምህርት ቤቶች ትኩረት በአብዛኛው የአካዳሚክ ዕውቀትን በማስተላለፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከንድፈ ሀሳብ እውቀት ባሻገር የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
‎በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች መማር ያለባቸው ለዕውቀት ብቻ ሳይሆን ያወቁትን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ ለመለወጥ፣ ከሌላው ጋር አብሮ መኖር የመሳሰሉ የትምህርት ምሶሶዎችን በማሟላት ሙሉ ሰው መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎የቦንጋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትምህርት ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ በመቻቻል ፣በመከባበር፣በመዋደድና አብሮ በመኖር ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገነሜ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የነገ አገር ተረካቢዎችን ለማፍራት በልዩ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች ፣ከተማሪዎች ከክልሉና ዞኑ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
‎በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍሎች በመጎብኘትና አሻራቸውን በማኖር ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀዋል።
በአዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት አዳሪ ትምህርት ቤቶች የነገዎቹ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነባባቸው ቦታዎች ናቸው።
‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርት ከማቅረብ ጎን ለጎን በጥሩ ባህሪ የተገነቡ ፣ሥነምግባር የተላበሱና በሙያቸው የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸውንም ክቡር አቶ ኮራ አስገንዝበዋል።
‎የትምህርት ቤቶች ትኩረት በአብዛኛው የአካዳሚክ ዕውቀትን በማስተላለፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከንድፈ ሀሳብ እውቀት ባሻገር የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
‎በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች መማር ያለባቸው ለዕውቀት ብቻ ሳይሆን ያወቁትን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ ለመለወጥ፣ ከሌላው ጋር አብሮ መኖር የመሳሰሉ የትምህርት ምሶሶዎችን በማሟላት ሙሉ ሰው መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎የቦንጋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትምህርት ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ በመቻቻል ፣በመከባበር፣በመዋደድና አብሮ በመኖር ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገነሜ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የነገ አገር ተረካቢዎችን ለማፍራት በልዩ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች ፣ከተማሪዎች ከክልሉና ዞኑ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
‎በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍሎች በመጎብኘትና አሻራቸውን በማኖር ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀዋል።
Dec 27, 2025 428
የሀገር ውስጥ ዜና

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ቡኢ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ።

መርሃ ግብሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል(ዶ/ር) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ስርዓቱ የገጠመንን የሞራል ስብራት ለማስተካከል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ሀገር በፍጥነት ማደግ ከፈለግን በትምህርት ላይ ትኩረት አድርገን መሥራት አለብን፤ በዚህም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት በሀሉም አካባቢ ለመሥጠት በኢትዮጵያ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
እስከዛው ድረስ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ የነገ ሀገር መሪዎችን ለማፍራት ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ትምህርት እያስጀመርን እንገኛለን ያሉ ሲሆን ።
ይህ ፕሮጀክት ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ማፍራት አለብን በሚል የተቋቋመ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት ብለዋል።
ተማሪዎችም በአለም ተወዳድረን ከማንም ሀገር እኩል መሆናችንን ማሳየት የምንችለው በእናንተ ነው፤ ለዛም ነው ከሁሉም የሀገራችን ክፍል አወዳድረን በመቀበል ልዩ ትኩረት ሰጥተን እያስተማርናችሁ ያለው ያሉ ሲሆን ያገኛችሁት እድል ማንም ያላገኘው በመሆኑ ጠንክራችሁ ለተያዘው ራዕይ መሳካት መማር አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።
አክለውም መምህራንና የትምህርት ቤቱ አስተዳደርም ከተማሪዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት የመማር ማስተማር ብቻ ሳይሆን ቤተሰባዊና ልጆቹ ሰው ሆነው እንዲወጡ የማድረግ ጭምር በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው በእነዚህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ወደ አደጉት ሀገራት ደረጃ ለማሳደግ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባር ፣ እርስ በርስ በመረዳዳት እንዲሁም ከማንም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ጠንክረው መማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም ተግባራት ውጤት ማየት ጀምረናል ያሉ ሲሆን ለዚህ አዳሪ ትምህርት ቤት ሰኬታማነትም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን ብለዋል።
በመድረኩም ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና ልምድ በመስጠት ድጋፍ ላደረገው የሀይሌ ማናስ አካዳሚ ምሰጋና ቀርቧል።
መርሃ ግብሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል(ዶ/ር) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ስርዓቱ የገጠመንን የሞራል ስብራት ለማስተካከል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ሀገር በፍጥነት ማደግ ከፈለግን በትምህርት ላይ ትኩረት አድርገን መሥራት አለብን፤ በዚህም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት በሀሉም አካባቢ ለመሥጠት በኢትዮጵያ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
እስከዛው ድረስ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ የነገ ሀገር መሪዎችን ለማፍራት ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ትምህርት እያስጀመርን እንገኛለን ያሉ ሲሆን ።
ይህ ፕሮጀክት ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ማፍራት አለብን በሚል የተቋቋመ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት ብለዋል።
ተማሪዎችም በአለም ተወዳድረን ከማንም ሀገር እኩል መሆናችንን ማሳየት የምንችለው በእናንተ ነው፤ ለዛም ነው ከሁሉም የሀገራችን ክፍል አወዳድረን በመቀበል ልዩ ትኩረት ሰጥተን እያስተማርናችሁ ያለው ያሉ ሲሆን ያገኛችሁት እድል ማንም ያላገኘው በመሆኑ ጠንክራችሁ ለተያዘው ራዕይ መሳካት መማር አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።
አክለውም መምህራንና የትምህርት ቤቱ አስተዳደርም ከተማሪዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት የመማር ማስተማር ብቻ ሳይሆን ቤተሰባዊና ልጆቹ ሰው ሆነው እንዲወጡ የማድረግ ጭምር በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው በእነዚህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ወደ አደጉት ሀገራት ደረጃ ለማሳደግ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባር ፣ እርስ በርስ በመረዳዳት እንዲሁም ከማንም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ጠንክረው መማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም ተግባራት ውጤት ማየት ጀምረናል ያሉ ሲሆን ለዚህ አዳሪ ትምህርት ቤት ሰኬታማነትም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን ብለዋል።
በመድረኩም ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና ልምድ በመስጠት ድጋፍ ላደረገው የሀይሌ ማናስ አካዳሚ ምሰጋና ቀርቧል።
Dec 27, 2025 548

ሚኒስትሮቻችን

ሚኒስቴር

ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

ሚኒስቴር ዴታ

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ