እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

የተረጋጋ ሀገር እንዲኖር በትምህርት ዘርፉ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሄድ ያስፈልጋል፤ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
Mar 01, 2026 1.1K
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
Feb 28, 2026 695
የሀገር ውስጥ ዜና

የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል።
ትምህርት ቤቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተገኝተው መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ዛሬ የተመረቀው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደ ሀገር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
ከለውጡ ወዲህ እንደ በፊቱ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉ ሲሆን በትምህርት ሴክተሩ ፕሮጀክት ጀምሮ በአጠረ ጊዜ መጨረስ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሴክተሩ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ወድቆ በመቆየቱ ከዚህ ለማላቀቅ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት እየተተገበሩ መሆኑንና በተለይም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ መስራትና መተማመን የሚችል ትውልድ ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ በመሆኑ በሁሉም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም ባለፉት አመታት ከ34ሺ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ 1452 ትምህርት ቤቶች በ726 ወረዳዎች በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር እንደሚገነቡ ጠቁመዋል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገትና ለዜጎች ከፍ ማለት ወሳኝ መሣሪያ በመሆኑ መንግስት በሪፎርሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የትምህርት ሴክተሩ እጅግ ስኬታማ ከሆኑ ተቋማት ውስጥ የሚጠቀስ መሆኑን አንስተው በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኘው ውጤት የሚደነቅ ነውም ብለዋል።
ይህ ትምህርት ቤትም ስታንዳርዱን ጠብቆ የተገነባ በመሆኑ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ጠብቆ በመከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሰባስቲያን ብራንስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች በትምህርት፣በጤና፣ በምግብ ዋስተናና በውሃ አቅርቦት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ሰፊ እድል ይዞ የመጣ በመሆኑ ውጤታማ ለመሆን ተማሪዎች ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል።
ትምህርት ቤቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተገኝተው መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ዛሬ የተመረቀው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደ ሀገር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
ከለውጡ ወዲህ እንደ በፊቱ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉ ሲሆን በትምህርት ሴክተሩ ፕሮጀክት ጀምሮ በአጠረ ጊዜ መጨረስ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሴክተሩ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ወድቆ በመቆየቱ ከዚህ ለማላቀቅ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት እየተተገበሩ መሆኑንና በተለይም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ መስራትና መተማመን የሚችል ትውልድ ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ በመሆኑ በሁሉም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም ባለፉት አመታት ከ34ሺ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ 1452 ትምህርት ቤቶች በ726 ወረዳዎች በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር እንደሚገነቡ ጠቁመዋል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገትና ለዜጎች ከፍ ማለት ወሳኝ መሣሪያ በመሆኑ መንግስት በሪፎርሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የትምህርት ሴክተሩ እጅግ ስኬታማ ከሆኑ ተቋማት ውስጥ የሚጠቀስ መሆኑን አንስተው በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኘው ውጤት የሚደነቅ ነውም ብለዋል።
ይህ ትምህርት ቤትም ስታንዳርዱን ጠብቆ የተገነባ በመሆኑ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ጠብቆ በመከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሰባስቲያን ብራንስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች በትምህርት፣በጤና፣ በምግብ ዋስተናና በውሃ አቅርቦት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ሰፊ እድል ይዞ የመጣ በመሆኑ ውጤታማ ለመሆን ተማሪዎች ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።
Feb 27, 2026 653
የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን '' አድዋ 130፣ ከአኩሪ ታሪክ፣ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል አገራዊ መሪ ቃል አክብረዋል።
‎የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ነጻነት ህያው ተምሳሌት በመሆኑ አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነትና ላጎናጸፉን ድል ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
‎ትምህርት ለምናደርገው የእድገትና የብልጽግና ጉዞ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ጅምር ስራዎቻችንን አልቆ በመፈጸም እንደሚገባ ክብርት ሚኒስትር ደኤታ አስገንዝበዋል።
‎አገራችን ለዜጎቿ የተመቸችና የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች የበኩላቸውን ድርሻ በላቀ የአገር ፍቅርና ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ክብርት ወ/ሮ አየለች አንስተዋል።
‎የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከመሠረቱ በህጻናት ላይ መስራት የሚገባን መሆኑን በመረዳት ለህጻት ትምህርት የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
‎ዳር ድንበሮቻችንን ለመጠበቅና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ለማዝለቅ አንድነታችንን ማጠናከር እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።
‎የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ለአንድነታችንና ለብሔራዊ ጥቅማችን ባለው ፋይዳ ላይ ግንዛቤ መፍጠር የክብረ በዓሉ ዓላማ መሆኑን አስተው አድዋ በዓለም ታሪክ አፍሪካዊት አገር ቅኝ ግዛትን በጦር ኃይል ያሸነፈችበትና በደማቅ ቀለም የተጻፈ ታሪካዊ ተምሳሌት የሆነችበት አኩሪ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ይማም በበኩላቸው የአድዋ ድል ብሔራዊ የአንድነትና የአሸናፊነት ምልክት መሆኑን አስረድተዋል።
‎የብሄራዊ ጥቅም የመጀመሪያው መነሻ ሉዓላዊነት በመሆኑ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ዜጎች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባም ገልጸዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ በተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን '' አድዋ 130፣ ከአኩሪ ታሪክ፣ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል አገራዊ መሪ ቃል አክብረዋል።
‎የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ነጻነት ህያው ተምሳሌት በመሆኑ አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነትና ላጎናጸፉን ድል ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
‎ትምህርት ለምናደርገው የእድገትና የብልጽግና ጉዞ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ጅምር ስራዎቻችንን አልቆ በመፈጸም እንደሚገባ ክብርት ሚኒስትር ደኤታ አስገንዝበዋል።
‎አገራችን ለዜጎቿ የተመቸችና የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች የበኩላቸውን ድርሻ በላቀ የአገር ፍቅርና ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ክብርት ወ/ሮ አየለች አንስተዋል።
‎የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከመሠረቱ በህጻናት ላይ መስራት የሚገባን መሆኑን በመረዳት ለህጻት ትምህርት የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
‎ዳር ድንበሮቻችንን ለመጠበቅና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ለማዝለቅ አንድነታችንን ማጠናከር እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።
‎የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ለአንድነታችንና ለብሔራዊ ጥቅማችን ባለው ፋይዳ ላይ ግንዛቤ መፍጠር የክብረ በዓሉ ዓላማ መሆኑን አስተው አድዋ በዓለም ታሪክ አፍሪካዊት አገር ቅኝ ግዛትን በጦር ኃይል ያሸነፈችበትና በደማቅ ቀለም የተጻፈ ታሪካዊ ተምሳሌት የሆነችበት አኩሪ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ይማም በበኩላቸው የአድዋ ድል ብሔራዊ የአንድነትና የአሸናፊነት ምልክት መሆኑን አስረድተዋል።
‎የብሄራዊ ጥቅም የመጀመሪያው መነሻ ሉዓላዊነት በመሆኑ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ዜጎች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባም ገልጸዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ በተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Feb 27, 2026 659
የሀገር ውስጥ ዜና

እንደ ሀገር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ባልሆነባቸው ወረዳዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የትምህርት ቤት ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ይገኛል።

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለሟሟላትና ለማሻሻል በቀረጸው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ነጻና የግዴታ ትምህርት እንዲሆን በማመላከት ከ34000 በላይ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት እነዚህ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም የነበረውን ክፍተት በሚፈለገው ልክ መሙላት ባለመቻሉ በርካታ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፤ ይንንም ለመቅረፍና ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በዚህም ‎ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ያልሆነባቸው አካባቢዎችና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወረዳዎች ልየታ መደረጉም ተገልጿል።
በነዚህ በተለዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር በውጤት ተኮር የገንዘብ ድጋፍ ስርዓት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ግንባታውን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከሚገነቡት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የዋጋ ጥናት 726ቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ ይሆናል። እነዚህ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት ክልሉ በተጠቀሱት ወረዳዎች ወይም አካባቢዎች ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰራው ልክ በክልሉ በጀት ወይንም ከማህበረሰቡ አሰባስቦ መገንባት የሚችል ከሆነ ብቻ ነው።
በዚህም በቀጣይ 6 ወራት ትምህርት ሚኒስቴር 726 እንዲሁም ክልሎች በተመሳሳይ 726 በአጠቃላይ 1452 የሚደርሱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ዲዛይን የተሰራ ሲሆን እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ መጠነኛ ለውጥ እንዲኖራቸው እንደሚደረግና ቢያንስ ሁለት የመማሪያ ፣ የመመገቢያ ፣ የህጻናት ማረፊያ ፣ የመምህራን ቢሮ፣ የመጸዳጃ ክፍሎችና ህጻናትን ለፈጠራ በማነሳሳት ሁለንተናዊ እድገታቸው ላይ አወንታዊ ሚና የሚጫወቱባቸው የመጫወቻ ቦታዎች እንደሚኖራቸው ተደርጎ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።
‎የእነዚህ ትምህርት ቤቶቹ መገንባት ሁሉም የኢትዮጵያ ህጻናት አንደኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ዓመት የቅድመ አንደኛ ደረጃ የዝግጁነት ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውም ይሆናል።
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለሟሟላትና ለማሻሻል በቀረጸው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ነጻና የግዴታ ትምህርት እንዲሆን በማመላከት ከ34000 በላይ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት እነዚህ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም የነበረውን ክፍተት በሚፈለገው ልክ መሙላት ባለመቻሉ በርካታ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፤ ይንንም ለመቅረፍና ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በዚህም ‎ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ያልሆነባቸው አካባቢዎችና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወረዳዎች ልየታ መደረጉም ተገልጿል።
በነዚህ በተለዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር በውጤት ተኮር የገንዘብ ድጋፍ ስርዓት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ግንባታውን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከሚገነቡት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የዋጋ ጥናት 726ቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ ይሆናል። እነዚህ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት ክልሉ በተጠቀሱት ወረዳዎች ወይም አካባቢዎች ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰራው ልክ በክልሉ በጀት ወይንም ከማህበረሰቡ አሰባስቦ መገንባት የሚችል ከሆነ ብቻ ነው።
በዚህም በቀጣይ 6 ወራት ትምህርት ሚኒስቴር 726 እንዲሁም ክልሎች በተመሳሳይ 726 በአጠቃላይ 1452 የሚደርሱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ዲዛይን የተሰራ ሲሆን እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ መጠነኛ ለውጥ እንዲኖራቸው እንደሚደረግና ቢያንስ ሁለት የመማሪያ ፣ የመመገቢያ ፣ የህጻናት ማረፊያ ፣ የመምህራን ቢሮ፣ የመጸዳጃ ክፍሎችና ህጻናትን ለፈጠራ በማነሳሳት ሁለንተናዊ እድገታቸው ላይ አወንታዊ ሚና የሚጫወቱባቸው የመጫወቻ ቦታዎች እንደሚኖራቸው ተደርጎ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።
‎የእነዚህ ትምህርት ቤቶቹ መገንባት ሁሉም የኢትዮጵያ ህጻናት አንደኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ዓመት የቅድመ አንደኛ ደረጃ የዝግጁነት ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውም ይሆናል።
Feb 23, 2026 637
የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ለአይነ ስውራን የተዘጋጁ የ2ኛ ደረጃ የብሬል መጽሐፍት እየተጓጓዙ ነው።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመጀመሪያው ዙር ለስርጭት የተዘጋጁ የብሬል መጽሀፍቱን የስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
‎ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመጽሐፍቱን ስርጭት ሂደት ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት፣አግባብነት ፣ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛል ብለዋል።
‎ከሪፎርም ስራዎች መካከልም የተሻሻለውን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መነሻ በማድረግ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ገልጸዋል።
‎ተግባራዊ በተደረገው ሥርዓተ ትምህርት መሠረትም ተማሪዎችና መምህራን የሚገለገሉባቸውን የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሀፍት አንድ ለአንድ ለማድረስ ሲሰራ መቆየቱንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል።
‎ሁሉም ዜጎች የመማርና የመማሪያ ግብዓቶችን ማግኘት መብት እንዳላቸው ያስገነዘቡት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ዜጎች በሁሉም ረገድ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
‎ለስርጭት የተዘጋጁት የብሬል መጽሐፍት አይስውራን ተማሪዎች በቂ የመማሪያ መጽሐፍት አግኝተው ራሳቸውን በማብቃት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል እድል እንዲያገኙና በእውቀትና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲገኙ እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።
‎የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከ 23.9 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው እየተሰራጩና እየተጓጓዙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
‎የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በበኩላቸው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሂደት ለስርጭት የተዘጋጁት የ2ኛ ደረጃ የብሬል መማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት በስድስት (6) የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
‎የብሬል መጽሀፍቱ ለሁሉም ክልል አይነ ስውራን ተማሪዎች መታተማቸውን የገለጹት ወ/ሮ ዛፉ በአሁኑ ወቅት ታትመው የተጠናቀቁት የብሬል መጽሐፍት ከማዕከል ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከሰኞ ጀምሮ እንደሚጓጓዙ ጠቁመዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመጀመሪያው ዙር ለስርጭት የተዘጋጁ የብሬል መጽሀፍቱን የስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
‎ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመጽሐፍቱን ስርጭት ሂደት ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት፣አግባብነት ፣ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛል ብለዋል።
‎ከሪፎርም ስራዎች መካከልም የተሻሻለውን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መነሻ በማድረግ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ገልጸዋል።
‎ተግባራዊ በተደረገው ሥርዓተ ትምህርት መሠረትም ተማሪዎችና መምህራን የሚገለገሉባቸውን የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሀፍት አንድ ለአንድ ለማድረስ ሲሰራ መቆየቱንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል።
‎ሁሉም ዜጎች የመማርና የመማሪያ ግብዓቶችን ማግኘት መብት እንዳላቸው ያስገነዘቡት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ዜጎች በሁሉም ረገድ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
‎ለስርጭት የተዘጋጁት የብሬል መጽሐፍት አይስውራን ተማሪዎች በቂ የመማሪያ መጽሐፍት አግኝተው ራሳቸውን በማብቃት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል እድል እንዲያገኙና በእውቀትና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲገኙ እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።
‎የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከ 23.9 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው እየተሰራጩና እየተጓጓዙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
‎የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በበኩላቸው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሂደት ለስርጭት የተዘጋጁት የ2ኛ ደረጃ የብሬል መማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት በስድስት (6) የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
‎የብሬል መጽሀፍቱ ለሁሉም ክልል አይነ ስውራን ተማሪዎች መታተማቸውን የገለጹት ወ/ሮ ዛፉ በአሁኑ ወቅት ታትመው የተጠናቀቁት የብሬል መጽሐፍት ከማዕከል ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከሰኞ ጀምሮ እንደሚጓጓዙ ጠቁመዋል።
Feb 16, 2026 633

ሚኒስትሮቻችን

ሚኒስቴር

ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

ሚኒስቴር ዴታ

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ