እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት አገልግሎትን ከትርፍ ጋር ብቻ አያይዞ መሥራት ሀገርን እንደሚጎዳ ተገለጻ፡፡

የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላይ አገልግሎት እየሰጡ ባሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባካሄደው የዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ዙሪያ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት አገልግሎትን ከትርፍ ጋር ብቻ አያይዞ መሥራት ሀገርን እንደሚጎዳ ገልጸዋል፡፡
መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተጠናው ጥናት መሠረት በተካሄደውና በቀጣይ በሚካሄደው ምዘና ዝቅተኛ የምዘና መስፈርቶችን የማያሟሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሥርዓቱ እንዲወጡ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲጫወቱ ከሀገር ወቅታዊና የወደፊት ፍላጎት እንዲሁም ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በመቃኘት መምራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ አክለውም ይህ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የተጀመረው የብቃት ምዘና ሥራ ያለ ምንም ማዳላት በተመሳሳይ መልኩ በመንግሥት ተቋማት ላይም ተግባራዊ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው በበኩላቸው ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በዳግም ምዝገባና አስፈላጊነቱ ላይ ውይይት ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ተገቢውን መስፈርት እንዲያሟሉ ተጨማሪ ጊዜ ከተሰጣቸው ተቋማት መካከል ዕድሉን ተጠቅመው መሻሻል ያሳዩ ተቋማት እንዳሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ህይወት አሰፋ ዳግም ምዝገባ ተቋማት ተዛማጅ ካልሆኑ የንግድ መስኮች ጋር ተቀላቅለው እንዳይሰሩ ፣ ህጋዊ የአሰራር ስርዓት ተከትለው እንዲሰሩ፣ በራሳቸዉ ህንጻ ወይም ሙሉ ህንጻ ተከራይተው ማስተማር እንዲችሉ፣ ሰነዶቻቸውን በአዲሱ የጥራት መስፈርት መሰረት እንዲከልሱ፣ የመምህራንን የትምህርት ዝግጅትና የቅጥር ሁኔታ በሚፈለገው ደረጃ እንዲያስተካክሉ፣ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ማህበረሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ የማበረታታት እና ተቋማዊ መዋቅራቸዉን በመገምገም ውጤታማ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና ሃላፈዎች ተገኝተው ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎች በከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላይ አገልግሎት እየሰጡ ባሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባካሄደው የዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ዙሪያ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት አገልግሎትን ከትርፍ ጋር ብቻ አያይዞ መሥራት ሀገርን እንደሚጎዳ ገልጸዋል፡፡
መንግስት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በተጠናው ጥናት መሠረት በተካሄደውና በቀጣይ በሚካሄደው ምዘና ዝቅተኛ የምዘና መስፈርቶችን የማያሟሉ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሥርዓቱ እንዲወጡ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲጫወቱ ከሀገር ወቅታዊና የወደፊት ፍላጎት እንዲሁም ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በመቃኘት መምራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ አክለውም ይህ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የተጀመረው የብቃት ምዘና ሥራ ያለ ምንም ማዳላት በተመሳሳይ መልኩ በመንግሥት ተቋማት ላይም ተግባራዊ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው በበኩላቸው ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በዳግም ምዝገባና አስፈላጊነቱ ላይ ውይይት ሲደረግ መቆየቱን ጠቅሰው የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ተገቢውን መስፈርት እንዲያሟሉ ተጨማሪ ጊዜ ከተሰጣቸው ተቋማት መካከል ዕድሉን ተጠቅመው መሻሻል ያሳዩ ተቋማት እንዳሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ህይወት አሰፋ ዳግም ምዝገባ ተቋማት ተዛማጅ ካልሆኑ የንግድ መስኮች ጋር ተቀላቅለው እንዳይሰሩ ፣ ህጋዊ የአሰራር ስርዓት ተከትለው እንዲሰሩ፣ በራሳቸዉ ህንጻ ወይም ሙሉ ህንጻ ተከራይተው ማስተማር እንዲችሉ፣ ሰነዶቻቸውን በአዲሱ የጥራት መስፈርት መሰረት እንዲከልሱ፣ የመምህራንን የትምህርት ዝግጅትና የቅጥር ሁኔታ በሚፈለገው ደረጃ እንዲያስተካክሉ፣ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ማህበረሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ የማበረታታት እና ተቋማዊ መዋቅራቸዉን በመገምገም ውጤታማ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ፋይዳ ያለው መሆኑን አንስተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና ሃላፈዎች ተገኝተው ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎች በከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል።
Aug 26, 2025 74
ማስታወቂያ

ማስታዋቂያ

በ 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ እንዲደረግላችሁ የምትፈልጉ ተመሳሳይ ጾታ መንትዮች፣ የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው ተማሪዎች የ 2017 ዓ.ም 12ኛ መልቀቂያ ፈተና ውጤት እስኪገለጽ ድረስ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።
የሚያስፈልጉ ሰነዶች
1. ለተመሳሳይ ጾታ መንትያ አመልካቾች
1.1. የሁለቱም አመልካቾች የልደት ካርድ
1.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
2. የሚያጠቡ እናት አመልካቾች
2.1. ስድስት (6) ወር ያልሞላው የህጻኑ/ኗ የክትባት ካርድ
2.2. ከተማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3. የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው አመልካቾች
3.1. ከመንግስት ሆስፒታሎች የቦርድ ወሳኔ የተሰጠበት የህክምና የምስክር ወረቀት
3.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ የመያስፈልጉ መሆኑን እንገልጻለን።
በ 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ እንዲደረግላችሁ የምትፈልጉ ተመሳሳይ ጾታ መንትዮች፣ የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው ተማሪዎች የ 2017 ዓ.ም 12ኛ መልቀቂያ ፈተና ውጤት እስኪገለጽ ድረስ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።
የሚያስፈልጉ ሰነዶች
1. ለተመሳሳይ ጾታ መንትያ አመልካቾች
1.1. የሁለቱም አመልካቾች የልደት ካርድ
1.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
2. የሚያጠቡ እናት አመልካቾች
2.1. ስድስት (6) ወር ያልሞላው የህጻኑ/ኗ የክትባት ካርድ
2.2. ከተማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3. የተለያዩ የጤና ዕክል ያለባቸው አመልካቾች
3.1. ከመንግስት ሆስፒታሎች የቦርድ ወሳኔ የተሰጠበት የህክምና የምስክር ወረቀት
3.2. ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ የመያስፈልጉ መሆኑን እንገልጻለን።
Aug 23, 2025 87
የሀገር ውስጥ ዜና

በሀዋሳ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገራዊ ምክክር መድረክ የ2018 ዓ.ም የቁልፍ ተግባራት ውጤት አመላካች መለኪያዎች ላይ የጋራ ስምምነት በመፈራረም ተጠናቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ለሁለት ቀናት በሀዋሳ ከተማ ሲያካሄድ የነበረው የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገራዊ የምክክር ከሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ቢሮዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የቁልፍ ተግባራት ውጤት አመላካቾችን የስምምነት ሰነድ በመፈራረም አጠናቋል።
መድረኩ በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በጥልቀት የተመከረበትና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከመግባባት የተደረሰበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት ተሳትፎ፣ ጥራትና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በ2017 የትምህርት ዘመን የተገኙ ስኬቶችን በማስፋትና በማስቀጠል በመጭው አመት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መድረኩ በመምከር አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑን ገልፀዋል።
በዘርፉ የአፈጻጸም ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች በመሻገር በ2018 የትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚደረገውን ጥረትም እንዲሁ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የተመከረበት እንደሆነም ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የትምህርት ለትውልድ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ አንደኛ ትምህርት፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር አቅም ግንባታ፣ ዲጂታይዜሽን እንዲሁም የወንድና ሴት ተማሪዎችን ምጥጥን አስጠብቆ የመሄድና ሌሎች መሰል የሪፎርም ስራዎች ላይ ሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተዘጋጁ የተለያዩ ረቂቅ ደንቦች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ደንቦቹ ሀገራዊ ሁኔታውንና የህዝብ ፍላጎትን ያማከሉ እንዲሆኑ በቀጣይ ግብዓት የማሰባሰብ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል።
የትምህርት ሚኒስቴር ለሁለት ቀናት በሀዋሳ ከተማ ሲያካሄድ የነበረው የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገራዊ የምክክር ከሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ቢሮዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የቁልፍ ተግባራት ውጤት አመላካቾችን የስምምነት ሰነድ በመፈራረም አጠናቋል።
መድረኩ በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በጥልቀት የተመከረበትና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከመግባባት የተደረሰበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት ተሳትፎ፣ ጥራትና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በ2017 የትምህርት ዘመን የተገኙ ስኬቶችን በማስፋትና በማስቀጠል በመጭው አመት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መድረኩ በመምከር አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑን ገልፀዋል።
በዘርፉ የአፈጻጸም ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶች በመሻገር በ2018 የትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚደረገውን ጥረትም እንዲሁ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የተመከረበት እንደሆነም ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ አያይዘው ገልጸዋል።
የትምህርት ለትውልድ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ አንደኛ ትምህርት፣ የስርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር አቅም ግንባታ፣ ዲጂታይዜሽን እንዲሁም የወንድና ሴት ተማሪዎችን ምጥጥን አስጠብቆ የመሄድና ሌሎች መሰል የሪፎርም ስራዎች ላይ ሁሉም የክልልና ከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተዘጋጁ የተለያዩ ረቂቅ ደንቦች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ደንቦቹ ሀገራዊ ሁኔታውንና የህዝብ ፍላጎትን ያማከሉ እንዲሆኑ በቀጣይ ግብዓት የማሰባሰብ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል።
Aug 22, 2025 35
የሀገር ውስጥ ዜና

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በውጭ ሀገር ካሉ አቻ ተቋማት ጋር የሚያደርጓቸውን ስምምነቶች አፈጻጸም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ተጠየቀ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ አስተባባሪነት ኢንሃ ከተሰኘ የኮሪያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

በስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትብብር ስምምነቱ በአቬሽን ሳይንስ፣ ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ እና ስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራሞችን በማጠናከር እንደሆነም ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የአቬሽን ሳይንስ እና ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለማጠናከር ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን ኢንሃ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ፕሮፌሰር ሂቸንግ ኮህ እና ጅማ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ደግሞ አቶ ኤፍሬም ዋቅጅራ ተፈራርመዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራምን ለማጠናከር ከአዲሰ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ከማል ኢብራሂም ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዶቹ የሚያተኩሩባቸው ቁልፍ ጉዳዮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና፣ ምርምር እና የተማሪዎችና መምህራን ልውውጥ ከትብብር ማዕቀፎቹ መካከል ዋና ዋናዎቹ እንደሚሆኑም ተገልጿል።
የማፈራረም ሂደቱን የመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የትብብር ማዕቀፎቹ በሶስቱም የትምህርት ፕሮግራሞች ሀገራችን ብቁ ባለሙያዎችን እንድታፈራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ጠቁመው ተቋማቱ በስምምነቱ መሰረት ለውጥ ለማምጣት ጠንክረው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ሶስቱም ተቋማት ተቋሞቻቸውን በመወከል የወሰዱትን የጋራ ሀላፊነትና አደራ በሚገባ እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
በስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትብብር ስምምነቱ በአቬሽን ሳይንስ፣ ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ እና ስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራሞችን በማጠናከር እንደሆነም ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የአቬሽን ሳይንስ እና ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለማጠናከር ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን ኢንሃ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ፕሮፌሰር ሂቸንግ ኮህ እና ጅማ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ደግሞ አቶ ኤፍሬም ዋቅጅራ ተፈራርመዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን የስማርት ሲቲ ትምህርት ፕሮግራምን ለማጠናከር ከአዲሰ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረመ ሲሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ከማል ኢብራሂም ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዶቹ የሚያተኩሩባቸው ቁልፍ ጉዳዮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና፣ ምርምር እና የተማሪዎችና መምህራን ልውውጥ ከትብብር ማዕቀፎቹ መካከል ዋና ዋናዎቹ እንደሚሆኑም ተገልጿል።
የማፈራረም ሂደቱን የመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የትብብር ማዕቀፎቹ በሶስቱም የትምህርት ፕሮግራሞች ሀገራችን ብቁ ባለሙያዎችን እንድታፈራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸውን ጠቁመው ተቋማቱ በስምምነቱ መሰረት ለውጥ ለማምጣት ጠንክረው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ሶስቱም ተቋማት ተቋሞቻቸውን በመወከል የወሰዱትን የጋራ ሀላፊነትና አደራ በሚገባ እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
Aug 22, 2025 43
የሀገር ውስጥ ዜና

እንደ ሀገር ፕሮጀክቶች ጀምሮ በፍጥነት ማጠናቀቅ በትምህርት ቤቶችም ባህል እየሆነ መምጣቱ ተገለፀ።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ተሳታፊዎች በሲዳማ ክልል ያለውን የትምህርት እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በትምህርት ቤቶቹ ተገኝተው ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀው የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ገልፀዋል።
በተለይም በወንዶ ገነት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገነባው የመማሪያ ህንፃ በ8 ወር ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት እየሠጠ መሆኑን ተመልክተዋል።
ይህም እንደ ሀገር ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ የሚለው ባህል እየሆነ መምጣቱን ያሳያል ያሉ ሲሆን ሌሎች ክልሎችም ከዚህ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ በበኩላቸው በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የሲዳማ ተሃድሶ በሚል የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል የተሠሩ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በተለይም እንደ ክልል ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተመሳሳይ ስታንዳርድ ያላቸው 78 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በአዲስ መገንባት መቻሉን ገልፀዋል።
የጉብኝቱ ዓላማም በክልሎች መካከል ልምድ መለዋወጥ መሆኑም ተገልጿል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ተሳታፊዎች በሲዳማ ክልል ያለውን የትምህርት እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በትምህርት ቤቶቹ ተገኝተው ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀው የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ገልፀዋል።
በተለይም በወንዶ ገነት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገነባው የመማሪያ ህንፃ በ8 ወር ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት እየሠጠ መሆኑን ተመልክተዋል።
ይህም እንደ ሀገር ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ የሚለው ባህል እየሆነ መምጣቱን ያሳያል ያሉ ሲሆን ሌሎች ክልሎችም ከዚህ ልምድ ሊወስዱ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ በበኩላቸው በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የሲዳማ ተሃድሶ በሚል የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል የተሠሩ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በተለይም እንደ ክልል ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተመሳሳይ ስታንዳርድ ያላቸው 78 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በአዲስ መገንባት መቻሉን ገልፀዋል።
የጉብኝቱ ዓላማም በክልሎች መካከል ልምድ መለዋወጥ መሆኑም ተገልጿል።
Aug 22, 2025 39
የሀገር ውስጥ ዜና

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገር አቀፍ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የዘርፉ መሪ ተዋንያኖችን ያሰባሰበው የምክክር መድረክ የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም የሚገመገምበትና የ2018 ዓ.ም እቅድ ላይ በመምከር የለውጥ ስራዎችን በላቀ ትጋት ለማስቀጠል ስምምነት የሚፈጸምበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርትን ለዜጎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድ ያሉ ጅምር ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ አስገነዝበዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመንግስት ብቻ በሚደረጉ ድጋፍና ጥረቶች የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ የማይቻል በመሆኑ በማህበረሰቡንና በሌሎች ባለድርሻ አካላት በትምህርት ለትውልድ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንዳለባቸው አሰገንዝበው በዚህ ረገድ የክልልና ከተማ አስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው መንግሥት ለሁሉም ዜጐች የምትመች፣ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት፣ የልማትና የብልጽግና ተስፋ የሚታይባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተለያዩ የለውጥ መርሃ ግብሮችን በመንደፍ በርካታ ሥራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ያብራሩ ሲሆን ከእነዚህ የለውጥ መርሃ ግብሮች አንዱ የትምህርት ዘርፉ የለውጥ መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸው በዚህም በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር አያይዘው የአምስት አመት የልማት መርሃ ግብር እንዲሁም የስድስተኛውን የትምህርት ልማት መርሃ ግብር የሚጠናቀቅበት ወቅት በመሆኑ የ2018 ዓ.ም እቅዶቻችንን ስኬታማ ለማድረግ መንደርደሪያ መሆኑን አብራርተዋል
ክቡር አቶ በየነ በራሶ የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በክልሉ ውስጥ በመንግስትና በማህበረሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ዋና ዋና የትምህርት ልማት ስራዎችን አብራርተዋል።
መድረኩ የተገኙ ስኬቶች ይበልጥ ለማዳበር ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በልምድ ልውውጥና ሌሎች ስልቶችን በመንደፍ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑም ጭምር ተገልጿል።
የዘርፉ መሪ ተዋንያኖችን ያሰባሰበው የምክክር መድረክ የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም የሚገመገምበትና የ2018 ዓ.ም እቅድ ላይ በመምከር የለውጥ ስራዎችን በላቀ ትጋት ለማስቀጠል ስምምነት የሚፈጸምበት መሆኑ ተመላክቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርትን ለዜጎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድ ያሉ ጅምር ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ አስገነዝበዋል።
ሚንስትሩ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመንግስት ብቻ በሚደረጉ ድጋፍና ጥረቶች የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ የማይቻል በመሆኑ በማህበረሰቡንና በሌሎች ባለድርሻ አካላት በትምህርት ለትውልድ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንዳለባቸው አሰገንዝበው በዚህ ረገድ የክልልና ከተማ አስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው መንግሥት ለሁሉም ዜጐች የምትመች፣ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት፣ የልማትና የብልጽግና ተስፋ የሚታይባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የተለያዩ የለውጥ መርሃ ግብሮችን በመንደፍ በርካታ ሥራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ያብራሩ ሲሆን ከእነዚህ የለውጥ መርሃ ግብሮች አንዱ የትምህርት ዘርፉ የለውጥ መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸው በዚህም በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
ክብርት ሚንስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር አያይዘው የአምስት አመት የልማት መርሃ ግብር እንዲሁም የስድስተኛውን የትምህርት ልማት መርሃ ግብር የሚጠናቀቅበት ወቅት በመሆኑ የ2018 ዓ.ም እቅዶቻችንን ስኬታማ ለማድረግ መንደርደሪያ መሆኑን አብራርተዋል
ክቡር አቶ በየነ በራሶ የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በክልሉ ውስጥ በመንግስትና በማህበረሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ዋና ዋና የትምህርት ልማት ስራዎችን አብራርተዋል።
መድረኩ የተገኙ ስኬቶች ይበልጥ ለማዳበር ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በልምድ ልውውጥና ሌሎች ስልቶችን በመንደፍ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑም ጭምር ተገልጿል።
Aug 21, 2025 61

ሚኒስትሮቻችን

MINISTER

ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

STATE MINISTER

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት

STATE MINISTER

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

STATE MINISTER

ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

የሚኒስትር አማካሪ ሚኒስቴር ዲኤታ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ