News Detail
Nov 11, 2025
36 views
የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል፤ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት
በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕ/ር ክንደያ ገ/ህይዎት የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
ፕ/ር ክንደያ አክለውም የትምህርት ማህበረሰቡ በ “ትምህርት ለትውልድ“ያሳየውን የላቀ ተሳትፎ በአዳሪ እና በሞዴል ት/ቤቶች ግንባታም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የሪፎርም ስራዎቻችንና አበይት ስራዎቻችንን በሚገባ ለይተን በዚህ የትምህርት ዘመን ውጤት ሊያመጡ በሚችል መልኩ መተግባር እንደሚገባም ተናገረዋል።