እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂን ለማሳደግ ያለመው የ2026 የኤድቴክ (EdTech) ሳምንት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂ (EdTech) ዘርፍን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
መርሃ ግብሩን በይፋ የከፈቱት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ማልማትና ጥቅም ላይ ማዋል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተለይም የትምህርት ስራውን የሚደግፉ ቴክኖሎጂዎች የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ጉልህ ሚና ያላቸው በመሆኑ በስፋት በማልማትና ተደራሽ በማድረግ ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ከዚህ አኳያም የለሙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተቋማዊ አሰራር (System) በመቀየር ረገድ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግርን ብሄራዊ አጀንዳ አድርጎ በትኩረት በማስፈጸም የማህበረሠቡን ተጠቃሚነት በመረጋገጥ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ያመላከቱት ሚኒስቴር ደኤታው በቀጣይም ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የኤድቴክ ፌሎውሺፕ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች የፈጠራ ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ይህም ለአዳዲስ የፈጠራ ስራ ባለቤት ለሆኑ ወጣቶች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
ይህ "የተቀናጀ የትምህርት ቴክኖሎጂ ሁሉን አቀፍ እና የሥርዓተ-ፆታ ምላሽ ሰጪ ለሆነ ትምህርት" በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በትምህርት ሚኒስቴር፣ በሪች ፎር ቼንጅ (Reach for Change) እና በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ትብብር የተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂ (EdTech) ዘርፍን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
መርሃ ግብሩን በይፋ የከፈቱት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ማልማትና ጥቅም ላይ ማዋል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተለይም የትምህርት ስራውን የሚደግፉ ቴክኖሎጂዎች የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ጉልህ ሚና ያላቸው በመሆኑ በስፋት በማልማትና ተደራሽ በማድረግ ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ከዚህ አኳያም የለሙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተቋማዊ አሰራር (System) በመቀየር ረገድ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግርን ብሄራዊ አጀንዳ አድርጎ በትኩረት በማስፈጸም የማህበረሠቡን ተጠቃሚነት በመረጋገጥ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ያመላከቱት ሚኒስቴር ደኤታው በቀጣይም ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የኤድቴክ ፌሎውሺፕ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች የፈጠራ ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ይህም ለአዳዲስ የፈጠራ ስራ ባለቤት ለሆኑ ወጣቶች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
ይህ "የተቀናጀ የትምህርት ቴክኖሎጂ ሁሉን አቀፍ እና የሥርዓተ-ፆታ ምላሽ ሰጪ ለሆነ ትምህርት" በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በትምህርት ሚኒስቴር፣ በሪች ፎር ቼንጅ (Reach for Change) እና በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ትብብር የተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።
Mar 26, 2026 217
የሀገር ውስጥ ዜና

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥራዎቻቸውን በእውነት፣ በሐቀኝነትና በታማኝነት ሊያከናውኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስገነዘቡ።

በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በተዘጋጁ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥራዎቻቸውን በእውነት፣ በሐቀኝነትና በታማኝነት ሊያከናውኑ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
‎በተቋማቱ የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ዓላማ ዩኒቨርስቲዎች ካሉባቸው ተለምዷዊ የአሰራር ልምዶች በማላቀቅ አርአያነት ባለው መልኩ ተልዕኳቸውን እንዲፈጽሙ ማስቻል መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ምልመላ የሚፈለጉ የአመራር ክህሎቶችን መሠረት ያደረገ ግልጽነትና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ ከዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ፣ ከኢንዱስትሪና የውጭ ዜጎችና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጭምር በሚጋብዝ መልኩ መዘጋጀቱንም ጠቅሰዋል።
‎ለዩኒቨርስቲዎች የሚመደበው የጥቅል በጀት ስሌት በቀመር ላይ እንዲሁም በግልጽነትና ተጠያቂነት ላይ በተመሠረተ አኳሃን ሊፈጸም እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
‎በየደረጃው ያሉ የዩዩኒቨርስቲ አመራሮች ለሥራቸው የሚያግዛቸውን የአመራር ስልጠና በማግኘት የአመራር ክህሎት እንዲያጎለብቱ የስልጠና ማዕከል መቋቋሙንም አመላክተዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጣቸውን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንዲችሉ እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የተዘጋጁት ደንብና መመሪያዎችም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ሥራዎቻቸውን በግልጸኝነትና ወጥ የሆነ አሰራር በማስፈን የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ደንብና መመሪያዎቹ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በሙያቸው የሰለጠኑ ብቁና ችሎታ ያላቸው የትምህርት አመራሮችን ወደ ስራ ማስገባት እንደሚያስችሉም ገልጸዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው በመድረኩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎ውይይት የተደረገባቸው ሰነዶች ተቋማቱ ያሉባቸውን ችግሮች በመፍታት ሀብቶቻቸውን በአግባቡ በማስተዳደር ለታለመለት ዓላማ እንዲያውሉና የትምህርት ጥራት እንዲያስጠብቁ እንደሚያስችሉም አስረድተዋል።
‎በመድረኩ ላይ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በተዘጋጁ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥራዎቻቸውን በእውነት፣ በሐቀኝነትና በታማኝነት ሊያከናውኑ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
‎በተቋማቱ የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ዓላማ ዩኒቨርስቲዎች ካሉባቸው ተለምዷዊ የአሰራር ልምዶች በማላቀቅ አርአያነት ባለው መልኩ ተልዕኳቸውን እንዲፈጽሙ ማስቻል መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ምልመላ የሚፈለጉ የአመራር ክህሎቶችን መሠረት ያደረገ ግልጽነትና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ ከዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ፣ ከኢንዱስትሪና የውጭ ዜጎችና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጭምር በሚጋብዝ መልኩ መዘጋጀቱንም ጠቅሰዋል።
‎ለዩኒቨርስቲዎች የሚመደበው የጥቅል በጀት ስሌት በቀመር ላይ እንዲሁም በግልጽነትና ተጠያቂነት ላይ በተመሠረተ አኳሃን ሊፈጸም እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
‎በየደረጃው ያሉ የዩዩኒቨርስቲ አመራሮች ለሥራቸው የሚያግዛቸውን የአመራር ስልጠና በማግኘት የአመራር ክህሎት እንዲያጎለብቱ የስልጠና ማዕከል መቋቋሙንም አመላክተዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጣቸውን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንዲችሉ እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የተዘጋጁት ደንብና መመሪያዎችም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ሥራዎቻቸውን በግልጸኝነትና ወጥ የሆነ አሰራር በማስፈን የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ደንብና መመሪያዎቹ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በሙያቸው የሰለጠኑ ብቁና ችሎታ ያላቸው የትምህርት አመራሮችን ወደ ስራ ማስገባት እንደሚያስችሉም ገልጸዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው በመድረኩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎ውይይት የተደረገባቸው ሰነዶች ተቋማቱ ያሉባቸውን ችግሮች በመፍታት ሀብቶቻቸውን በአግባቡ በማስተዳደር ለታለመለት ዓላማ እንዲያውሉና የትምህርት ጥራት እንዲያስጠብቁ እንደሚያስችሉም አስረድተዋል።
‎በመድረኩ ላይ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
Mar 23, 2026 219
የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና ኒውዝላንድ በትምህርቱ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደርጉ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አካላት በትምህርት ዘርፉ የነበራቸውን ትብብር አጠናክረው መቀጥል በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ውቅት የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለአምባሳደሯ አብርራተውላቸዋል።

እነዚህን የሪፎርም ተግባራት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግም ከሀገሪቱ የመልማት ፍላጎት ጋር አብረው በሚሄዱ አዳዲስ የትምህርት መስኮች፣ በከፍተኛ ትምህርት ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ልማት፣ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ግብዓት አቅርቦትና በመሳሰሉት ላይ የአጋር አካላትን ድጋፍ እንደሚፈልጉ ጠይቀዋል።

 

በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየተገበረቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራት የሚደነቁ መሆኑን ገልጸው ኒውዝላድ በትምህርቱ ዘርፍ የምታደርገውን ትብብር አጠናክራ መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

በተለይም በነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራን ልውውጥ፣ በመምህራን ስልጠናዎች፣ በትምህርት ቤት ምገባ የእርሻ ልማት፣ የባህል ልውውጥና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ለሚንስትሩ አብራርተውላቸዋል።

በስተመጨረሻም ሁለቱ ወገኖች በትምህርቱ ዘርፍ በሚኖራቸው ትብብር ዙሪያ ቀጣይ ውይይት ለማድርግና በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደርሰዋል።

 

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አካላት በትምህርት ዘርፉ የነበራቸውን ትብብር አጠናክረው መቀጥል በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ውቅት የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለአምባሳደሯ አብርራተውላቸዋል።

እነዚህን የሪፎርም ተግባራት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግም ከሀገሪቱ የመልማት ፍላጎት ጋር አብረው በሚሄዱ አዳዲስ የትምህርት መስኮች፣ በከፍተኛ ትምህርት ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ልማት፣ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ግብዓት አቅርቦትና በመሳሰሉት ላይ የአጋር አካላትን ድጋፍ እንደሚፈልጉ ጠይቀዋል።

 

በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየተገበረቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራት የሚደነቁ መሆኑን ገልጸው ኒውዝላድ በትምህርቱ ዘርፍ የምታደርገውን ትብብር አጠናክራ መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

በተለይም በነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራን ልውውጥ፣ በመምህራን ስልጠናዎች፣ በትምህርት ቤት ምገባ የእርሻ ልማት፣ የባህል ልውውጥና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ለሚንስትሩ አብራርተውላቸዋል።

በስተመጨረሻም ሁለቱ ወገኖች በትምህርቱ ዘርፍ በሚኖራቸው ትብብር ዙሪያ ቀጣይ ውይይት ለማድርግና በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደርሰዋል።

 

Mar 19, 2026 170
የሀገር ውስጥ ዜና

ሴቶችን በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደ ሀገር በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ከክብረዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ጥራቱን የጠበቀና ፍትሃዊ የትምህርት ተደራሽነትን በማረጋገጥ ሴቶችን በኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ እና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደ ሀገር በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩልነት ማረጋገጥ በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ አይተኬ ሚና ያለው መሆኑን በማንሳት እድሎችን አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም መንግስት የሴቶችን ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ በወሰዳቸው ቁርጠኛ እርምጃዎች ውጤቶች መታየት መጀመራቸውን ጠቁመው በተለይም ሴቶች በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ እንዲመደቡና የራሳቸውን እንዲሁም የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ እንዲወስኑ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን አብራርተዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ታምሩ በበኩላቸው ባደረጉት ገለፃ የሴቶች እኩልነት ጉዳይ የአንድ ወቅት ተግባር ሳይሆን ዘላቂ ትኩረት የሚሻ የሰብዓዊ መብትና የልማት ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።
በመጨረሻም በሁሉም የትምህርት እርከኖች የሚገኙ ሴት ተማሪዎችና በስራ ዓለም ያሉ ሴቶች ያላቸውን አቅም ተጠቅመው ለሀገር ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ከክብረዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ጥራቱን የጠበቀና ፍትሃዊ የትምህርት ተደራሽነትን በማረጋገጥ ሴቶችን በኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ እና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደ ሀገር በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩልነት ማረጋገጥ በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ አይተኬ ሚና ያለው መሆኑን በማንሳት እድሎችን አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም መንግስት የሴቶችን ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ በወሰዳቸው ቁርጠኛ እርምጃዎች ውጤቶች መታየት መጀመራቸውን ጠቁመው በተለይም ሴቶች በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ እንዲመደቡና የራሳቸውን እንዲሁም የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ እንዲወስኑ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን አብራርተዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ታምሩ በበኩላቸው ባደረጉት ገለፃ የሴቶች እኩልነት ጉዳይ የአንድ ወቅት ተግባር ሳይሆን ዘላቂ ትኩረት የሚሻ የሰብዓዊ መብትና የልማት ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።
በመጨረሻም በሁሉም የትምህርት እርከኖች የሚገኙ ሴት ተማሪዎችና በስራ ዓለም ያሉ ሴቶች ያላቸውን አቅም ተጠቅመው ለሀገር ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
Mar 18, 2026 178
የሀገር ውስጥ ዜና

የተረጋጋ ሀገር እንዲኖር በትምህርት ዘርፉ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሄድ ያስፈልጋል፤ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
Mar 01, 2026 1.4K
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
Feb 28, 2026 905

ሚኒስትሮቻችን

ሚኒስቴር

ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

ሚኒስቴር ዴታ

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ