Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education's Website

The FDRE Ministry of Education is a governmental institution headquartered in Arada Sub City, Addis Ababa, Ethiopia.

Our Recent News

Reads Our Latest News and Events

National News

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ቡኢ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ።

መርሃ ግብሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል(ዶ/ር) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ስርዓቱ የገጠመንን የሞራል ስብራት ለማስተካከል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ሀገር በፍጥነት ማደግ ከፈለግን በትምህርት ላይ ትኩረት አድርገን መሥራት አለብን፤ በዚህም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት በሀሉም አካባቢ ለመሥጠት በኢትዮጵያ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
እስከዛው ድረስ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ የነገ ሀገር መሪዎችን ለማፍራት ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ትምህርት እያስጀመርን እንገኛለን ያሉ ሲሆን ።
ይህ ፕሮጀክት ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ማፍራት አለብን በሚል የተቋቋመ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት ብለዋል።
ተማሪዎችም በአለም ተወዳድረን ከማንም ሀገር እኩል መሆናችንን ማሳየት የምንችለው በእናንተ ነው፤ ለዛም ነው ከሁሉም የሀገራችን ክፍል አወዳድረን በመቀበል ልዩ ትኩረት ሰጥተን እያስተማርናችሁ ያለው ያሉ ሲሆን ያገኛችሁት እድል ማንም ያላገኘው በመሆኑ ጠንክራችሁ ለተያዘው ራዕይ መሳካት መማር አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።
አክለውም መምህራንና የትምህርት ቤቱ አስተዳደርም ከተማሪዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት የመማር ማስተማር ብቻ ሳይሆን ቤተሰባዊና ልጆቹ ሰው ሆነው እንዲወጡ የማድረግ ጭምር በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው በእነዚህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ወደ አደጉት ሀገራት ደረጃ ለማሳደግ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባር ፣ እርስ በርስ በመረዳዳት እንዲሁም ከማንም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ጠንክረው መማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም ተግባራት ውጤት ማየት ጀምረናል ያሉ ሲሆን ለዚህ አዳሪ ትምህርት ቤት ሰኬታማነትም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን ብለዋል።
በመድረኩም ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና ልምድ በመስጠት ድጋፍ ላደረገው የሀይሌ ማናስ አካዳሚ ምሰጋና ቀርቧል።
መርሃ ግብሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል(ዶ/ር) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ስርዓቱ የገጠመንን የሞራል ስብራት ለማስተካከል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ሀገር በፍጥነት ማደግ ከፈለግን በትምህርት ላይ ትኩረት አድርገን መሥራት አለብን፤ በዚህም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት በሀሉም አካባቢ ለመሥጠት በኢትዮጵያ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
እስከዛው ድረስ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ የነገ ሀገር መሪዎችን ለማፍራት ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ትምህርት እያስጀመርን እንገኛለን ያሉ ሲሆን ።
ይህ ፕሮጀክት ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ማፍራት አለብን በሚል የተቋቋመ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት ብለዋል።
ተማሪዎችም በአለም ተወዳድረን ከማንም ሀገር እኩል መሆናችንን ማሳየት የምንችለው በእናንተ ነው፤ ለዛም ነው ከሁሉም የሀገራችን ክፍል አወዳድረን በመቀበል ልዩ ትኩረት ሰጥተን እያስተማርናችሁ ያለው ያሉ ሲሆን ያገኛችሁት እድል ማንም ያላገኘው በመሆኑ ጠንክራችሁ ለተያዘው ራዕይ መሳካት መማር አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።
አክለውም መምህራንና የትምህርት ቤቱ አስተዳደርም ከተማሪዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት የመማር ማስተማር ብቻ ሳይሆን ቤተሰባዊና ልጆቹ ሰው ሆነው እንዲወጡ የማድረግ ጭምር በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው በእነዚህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ወደ አደጉት ሀገራት ደረጃ ለማሳደግ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባር ፣ እርስ በርስ በመረዳዳት እንዲሁም ከማንም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ጠንክረው መማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም ተግባራት ውጤት ማየት ጀምረናል ያሉ ሲሆን ለዚህ አዳሪ ትምህርት ቤት ሰኬታማነትም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን ብለዋል።
በመድረኩም ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና ልምድ በመስጠት ድጋፍ ላደረገው የሀይሌ ማናስ አካዳሚ ምሰጋና ቀርቧል።
Dec 27, 2025 62
National News

የዩኒቨርስቲ የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥን አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤

የጅማ ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ጌንት የ25 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥናቸው አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል።
‎የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች እንደሀገር እሰከ 80 በመቶ የሚደርስ የክሊኒካል አገልግሎት ጫና እንዳለባቸው የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታትም አየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለዩኒቨርስቲው ህክምና ማዕከል የተደረገው የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የጅማ ዩኒቨርስቲን ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የጅማ ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ጌንት የ25 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥናቸው አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል።
‎የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች እንደሀገር እሰከ 80 በመቶ የሚደርስ የክሊኒካል አገልግሎት ጫና እንዳለባቸው የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታትም አየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለዩኒቨርስቲው ህክምና ማዕከል የተደረገው የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የጅማ ዩኒቨርስቲን ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
Dec 27, 2025 60
National News

የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በጂግጂጋ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላለፉ።

የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸው የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የጂግጂጋ የፌዴራል አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚንስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለአጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ መርሃ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም መንግስት የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታዋ በዚህ የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኛችሁ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ታሪካዊ በሆነው መርሃ ግብር የመጀመሪያዎቹ ተዋንያን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አያይዘውም ተማሪዎች ዓላማቸው ላይ ትኩረት በማድረግ በትምህርታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም ምሳሌ የሚሆኑ ዜጎች እንዲሆኑ፤ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እንደ ቤተሰብ ሆነው በታላቅ ሃላፊነት ተማሪዎችን በማገዝ ብቁ ዜጎችን እንዲያፈሩ አደራ ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር በማያያዝም እስካሁን በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድና ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ ስራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ በማስቀጠል ክፍተቶች እየተሞሉ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሄድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ መሃመድ አደን እና የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ፔሬዘዳንት ዶ/ር ሠይድ መሃመድ በመገኘት ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸው የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የጂግጂጋ የፌዴራል አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚንስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለአጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ መርሃ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም መንግስት የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታዋ በዚህ የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኛችሁ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ታሪካዊ በሆነው መርሃ ግብር የመጀመሪያዎቹ ተዋንያን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አያይዘውም ተማሪዎች ዓላማቸው ላይ ትኩረት በማድረግ በትምህርታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም ምሳሌ የሚሆኑ ዜጎች እንዲሆኑ፤ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እንደ ቤተሰብ ሆነው በታላቅ ሃላፊነት ተማሪዎችን በማገዝ ብቁ ዜጎችን እንዲያፈሩ አደራ ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር በማያያዝም እስካሁን በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድና ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ ስራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ በማስቀጠል ክፍተቶች እየተሞሉ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሄድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ መሃመድ አደን እና የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ፔሬዘዳንት ዶ/ር ሠይድ መሃመድ በመገኘት ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Dec 27, 2025 74
National News

ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የወደፊቱ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ሰብዕና የሚገነባባቸው ተቋማት መሆናቸው ተመላከተ፤ የቦንጋ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በአዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት አዳሪ ትምህርት ቤቶች የነገዎቹ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነባባቸው ቦታዎች ናቸው።
‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርት ከማቅረብ ጎን ለጎን በጥሩ ባህሪ የተገነቡ ፣ሥነምግባር የተላበሱና በሙያቸው የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸውንም ክቡር አቶ ኮራ አስገንዝበዋል።
‎የትምህርት ቤቶች ትኩረት በአብዛኛው የአካዳሚክ ዕውቀትን በማስተላለፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከንድፈ ሀሳብ እውቀት ባሻገር የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
‎በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች መማር ያለባቸው ለዕውቀት ብቻ ሳይሆን ያወቁትን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ ለመለወጥ፣ ከሌላው ጋር አብሮ መኖር የመሳሰሉ የትምህርት ምሶሶዎችን በማሟላት ሙሉ ሰው መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎የቦንጋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትምህርት ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ በመቻቻል ፣በመከባበር፣በመዋደድና አብሮ በመኖር ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገነሜ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የነገ አገር ተረካቢዎችን ለማፍራት በልዩ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች ፣ከተማሪዎች ከክልሉና ዞኑ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
‎በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍሎች በመጎብኘትና አሻራቸውን በማኖር ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀዋል።
በአዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት አዳሪ ትምህርት ቤቶች የነገዎቹ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነባባቸው ቦታዎች ናቸው።
‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርት ከማቅረብ ጎን ለጎን በጥሩ ባህሪ የተገነቡ ፣ሥነምግባር የተላበሱና በሙያቸው የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸውንም ክቡር አቶ ኮራ አስገንዝበዋል።
‎የትምህርት ቤቶች ትኩረት በአብዛኛው የአካዳሚክ ዕውቀትን በማስተላለፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከንድፈ ሀሳብ እውቀት ባሻገር የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
‎በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች መማር ያለባቸው ለዕውቀት ብቻ ሳይሆን ያወቁትን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ ለመለወጥ፣ ከሌላው ጋር አብሮ መኖር የመሳሰሉ የትምህርት ምሶሶዎችን በማሟላት ሙሉ ሰው መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎የቦንጋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትምህርት ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ በመቻቻል ፣በመከባበር፣በመዋደድና አብሮ በመኖር ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገነሜ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የነገ አገር ተረካቢዎችን ለማፍራት በልዩ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች ፣ከተማሪዎች ከክልሉና ዞኑ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
‎በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍሎች በመጎብኘትና አሻራቸውን በማኖር ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀዋል።
Dec 27, 2025 58
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የወሊሶ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመለከቱ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት የወሊሶ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበት ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አመራሮቹ የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍል፣ የተማሪዎች ዶርም፣ የመመገቢያ አዳራሽ ፣ የአስተዳደር ህንፃና ሌሎች ግንባታዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምልከታቸውም ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የተመለከቱ ሲሆን ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ተማሪዎችን ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የማዛወር ሥራ ይሰራል ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የወሊሶ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ እስኪደርስ ድረስ ተማሪዎች በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀጫሉ ካምፓስ በመቀበል በዛሬው እለት የመማር ማስተማር ሥራ ማስጀመሩ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት የወሊሶ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበት ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አመራሮቹ የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍል፣ የተማሪዎች ዶርም፣ የመመገቢያ አዳራሽ ፣ የአስተዳደር ህንፃና ሌሎች ግንባታዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምልከታቸውም ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የተመለከቱ ሲሆን ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ተማሪዎችን ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የማዛወር ሥራ ይሰራል ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የወሊሶ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ እስኪደርስ ድረስ ተማሪዎች በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀጫሉ ካምፓስ በመቀበል በዛሬው እለት የመማር ማስተማር ሥራ ማስጀመሩ ይታወሳል።
Dec 26, 2025 62
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አደረጉ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ ህይወት ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ዓመታት የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት ቢሰራም ከትምህርት ጥራት አንፃር የትምህርት ሥርዓቱ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይቷል ብለዋል።
በተጨማሪም ትምህርትና ፖለቲካ በመደበላለቃቸው የትምህርት ተቋማት የፖለቲካ ፍላጎት ማስጠበቂያ ተደርገው መቆየታቸውንም ሌላው ችግር መሆኑን አንስተዋል።
አሁን አለም እየሄደች ባለችበት መንገድ ተቋቁመን አብረን ለመቀጠልና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በዚህ መንገድ መቀጠል ስለማይቻል ችግሩን ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይ ዩኒቨርሲቲዎች እውነትና እውቀት የሚፈልቅባቸው በነፃነት ውይይት የሚደረግባቸው ዩኒቨርሳል ተቋማት መሆናቸውን ያነሱ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ኢትዮጵያ ባላት ፀጋዎች ዙሪያ ትርጉም ያላቸው ፈጠራ እና ጥናትና ምርምር የሚደረግባቸው ተቋማት ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቅሰው ተቋማቱም ለስራዎቻቸው የሚበረታቱበት ሥርዓት መፍጠር ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን የዩኒቨርሲቲ አመራር ምደባም ከመንደር ወጥቶ በውድድር እንዲሆን እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ ሲሆን ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ አብዛኞቹን ወደ ፖሊሲና ውጤታማነት እየተቀየሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተ ጀምሮ በርካታ ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የተናሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ውጤታማ እንዲሆን የበለጠ ለጥራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ ህይወት ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ዓመታት የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት ቢሰራም ከትምህርት ጥራት አንፃር የትምህርት ሥርዓቱ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይቷል ብለዋል።
በተጨማሪም ትምህርትና ፖለቲካ በመደበላለቃቸው የትምህርት ተቋማት የፖለቲካ ፍላጎት ማስጠበቂያ ተደርገው መቆየታቸውንም ሌላው ችግር መሆኑን አንስተዋል።
አሁን አለም እየሄደች ባለችበት መንገድ ተቋቁመን አብረን ለመቀጠልና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በዚህ መንገድ መቀጠል ስለማይቻል ችግሩን ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይ ዩኒቨርሲቲዎች እውነትና እውቀት የሚፈልቅባቸው በነፃነት ውይይት የሚደረግባቸው ዩኒቨርሳል ተቋማት መሆናቸውን ያነሱ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ኢትዮጵያ ባላት ፀጋዎች ዙሪያ ትርጉም ያላቸው ፈጠራ እና ጥናትና ምርምር የሚደረግባቸው ተቋማት ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቅሰው ተቋማቱም ለስራዎቻቸው የሚበረታቱበት ሥርዓት መፍጠር ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን የዩኒቨርሲቲ አመራር ምደባም ከመንደር ወጥቶ በውድድር እንዲሆን እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ ሲሆን ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ አብዛኞቹን ወደ ፖሊሲና ውጤታማነት እየተቀየሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተ ጀምሮ በርካታ ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የተናሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ውጤታማ እንዲሆን የበለጠ ለጥራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
Dec 26, 2025 67

Our Ministers

MINISTER

H.E Professor. Birhanu Nega

Ministry of Education

STATE MINISTER

H.E Mrs. Ayelech Eshete

General Education

STATE MINISTER

H.E Ato Kora Tushune

Higher Education

STATE MINISTER

Professor Kindeya Gebrehiwot

Advisor to the Ministry of Education

Organization structure

This is The Main Ministry Organization Structure Chart

General Education

Curriculum Development Executive

Head, Language and Co-curricular Education Curriculum Desk

Head, Social Science Education Curriculum Desk

Head, Natural Science Education Curriculum Desk

Head, Career and Technical Education Curriculum Desk

Teachers’ and Educational Leaders’ Development Executive

Head, Teachers’ and Educational Leaders Development Desk

Head, Education Language Development Desk

Head, STEAM DESK

Educational Program and Quality Improvement Executive

Head, Education Programs and Quality Improvement Desk

Head, Pastoralist and Special Needs Education Desk

Head, Education Infrastructure and Service Desk

Head, General Education Inspection Desk

Adult and Non-formal Education Programs Executive

Head, Adults’ Basic Education Desk

Head, Non-Formal and Lifelong Education Programs Desk

Higher Education

Academic Affairs Executive

Head, Competency and Quality Improvement Desk

Head, Curriculum and Programs Desk

Head, Teachers’ and Students’ Development Desk

Head, Private Higher Education Institutions Service Desk

Research and Community Engagement Executive

Head, Research and Extension Desk

Head, Research Ethics Desk

Head, Institutional Linkage and Technology Transfer Desk

Head, Community Engagement and Indigenous Knowledge Desk

Governance and Infrastructure Executive

Head, Administration Affairs Desk

Head, Institutional Structure and Leadership Desk

Head, Infrastructure and Input Desk

Head, Scholarship and Internationalization Desk

ICT and Digital Education Executive

Head, Education Multimedia Program Development Desk

Head, School Net ICT Desk

Head, Education Media Studio Operation and Administration Desk

Head, Network Technical Desk

Head, Network Operation Desk