Welcome to Ministry of Education Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Welcome to Ministry of Education Website

FDRE Ministry of Education is a Governmental Organization Headquartered in Arada sub-city, Addis Ababa, Ethiopia.

Our Recent News

Reads Our Latest News and Events

National News

ለዲጂታል ትምህርት (e-learning) ተደራሽነትና ጥራት የሚጠቅሙ አምስት የዲጂታል መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች ተመረቁ

ለዲጂታል ትምህርት (e-learning) ተደራሽነትና ጥራት የሚጠቅሙ አምስት የዲጂታል መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በድሬደዋ፣ በሀዋሳና በጅማ ዩኒቨርሲቲዎች ተመርቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ተወካይ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ የነዚህ ስቱዲዮዎች መገንባት መሰረታዊ ዓላማው ዩኒቨርስቲዎች የተሻሉ ባለሙያዎችን በመጠቀም ጥራቱን እና አግባብነቱን የጠበቀ የኤሌክትሮኒክ ኮርስ ቀረጻ ማካሄድ መሆኑንና ስቱዲዮ የተገነባላቸው ተቋማት በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የየራሳቸውን ስቱዲዮ እስኪያቋቁሙ ድረስ አገልግሎት መስጠት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡
በዚህ የዲጂታል መርሃ- ግብር የመምህራንን የኤሌክትሮኒክስ ትምህርት አሰጣጥ አቅምን ለመገንባት እና የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለማስተማር የታቀደ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም ለመማር ጊዜ የማይኖራቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሥራቸው ላይ ምንም ተጽዕኖ ሳይፈጠር ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን በነዚህ የመልቲ ዲጂታል እስቱዲዮ ግንባታ ሂደት ውስጥ የተሳታፉ አካላትን እስከ አሁን ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይ በሚሠሩ ሥራዎችም ላይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡
በአሜሪካ የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ዶ/ር ዩካኢ ምላምቦ (Yeukai Mlambo,Ph.D)የተመረቁት መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ረገድ ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚወስዱና በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያላቸውን የማስተማሪያ ግብዓቶችና መሳሪያዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዩካኢ ለውጡ ከልማዳዊ የማማር ማስማር ሂደት ወደ ድንበር፣ቦታና ጊዜ የማይገድበው ዲጂታል አለም የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ለዲጂታል ስቱዲዮው ከፍተኛ አስተዋጾ ካደረጉት አጋሮች መካከልም የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው የዚህ ዲጂታል ስቱዲዮ መገንባት የወደፊቱን የተማሪዎችንና የወጣቶቻችንን ሥራ ፈጣሪነት በማጎለበትና ሥራ አጥነትን ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ድርሻ ያለዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የተገነቡ ስቱዲዮዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትን በማሻሻል በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሀይል ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆኑን ጠቀሰው ስቱዲዮዎቹም እንዲገነቡ ለበረከቱት አስተዋጽኦ ትምህርት ሚኒስቴርን፣የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲንና የማስተር ካርድ ፋውንዴሽንን አመስግነዋል።
የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ እስቲዲዮ የተገነባላቸው የአራቱ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ከተገነቡ ስቱዲዮዎች በበይነመረብ ለታዳሚዎች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተገነባው ስቱዲዮም ተጎብኝቷል፡፡
ለዲጂታል ትምህርት (e-learning) ተደራሽነትና ጥራት የሚጠቅሙ አምስት የዲጂታል መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በድሬደዋ፣ በሀዋሳና በጅማ ዩኒቨርሲቲዎች ተመርቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ተወካይ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ የነዚህ ስቱዲዮዎች መገንባት መሰረታዊ ዓላማው ዩኒቨርስቲዎች የተሻሉ ባለሙያዎችን በመጠቀም ጥራቱን እና አግባብነቱን የጠበቀ የኤሌክትሮኒክ ኮርስ ቀረጻ ማካሄድ መሆኑንና ስቱዲዮ የተገነባላቸው ተቋማት በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የየራሳቸውን ስቱዲዮ እስኪያቋቁሙ ድረስ አገልግሎት መስጠት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡
በዚህ የዲጂታል መርሃ- ግብር የመምህራንን የኤሌክትሮኒክስ ትምህርት አሰጣጥ አቅምን ለመገንባት እና የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለማስተማር የታቀደ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም ለመማር ጊዜ የማይኖራቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሥራቸው ላይ ምንም ተጽዕኖ ሳይፈጠር ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን በነዚህ የመልቲ ዲጂታል እስቱዲዮ ግንባታ ሂደት ውስጥ የተሳታፉ አካላትን እስከ አሁን ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይ በሚሠሩ ሥራዎችም ላይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡
በአሜሪካ የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ዶ/ር ዩካኢ ምላምቦ (Yeukai Mlambo,Ph.D)የተመረቁት መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ረገድ ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚወስዱና በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያላቸውን የማስተማሪያ ግብዓቶችና መሳሪያዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዩካኢ ለውጡ ከልማዳዊ የማማር ማስማር ሂደት ወደ ድንበር፣ቦታና ጊዜ የማይገድበው ዲጂታል አለም የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ለዲጂታል ስቱዲዮው ከፍተኛ አስተዋጾ ካደረጉት አጋሮች መካከልም የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው የዚህ ዲጂታል ስቱዲዮ መገንባት የወደፊቱን የተማሪዎችንና የወጣቶቻችንን ሥራ ፈጣሪነት በማጎለበትና ሥራ አጥነትን ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ድርሻ ያለዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የተገነቡ ስቱዲዮዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትን በማሻሻል በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ሀይል ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆኑን ጠቀሰው ስቱዲዮዎቹም እንዲገነቡ ለበረከቱት አስተዋጽኦ ትምህርት ሚኒስቴርን፣የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲንና የማስተር ካርድ ፋውንዴሽንን አመስግነዋል።
የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ እስቲዲዮ የተገነባላቸው የአራቱ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ከተገነቡ ስቱዲዮዎች በበይነመረብ ለታዳሚዎች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተገነባው ስቱዲዮም ተጎብኝቷል፡፡
Mar 05, 2024 85
National News

በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡

በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን " ለሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለተሻለ ትውልድ ግንባታ!!" በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበዓሉ ላይ ተገኝተው የትምህርት ቤት ምገባ ወጪ ሳይሆን በመጪው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ የሚደረግ አዋጭና ዘላቂ የሰብዓዊ ልማት ኢንቨስትመንት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መርሃ-ግብሩ በአግባቡ ከተተገበረ የልጆችን አካላዊና አዕምሮኣዊ ዕድገት በማፋጠንና ጤንነታቸውን በመጠበቅ የተማሪዎችን የትምህርት ውጤታማነት እንዲሻሻል በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የትምህርት ቤት ምገባ እንደሃገር በመንግሰት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ያለና ከ6.2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የመንግስት አካላት፣የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ታዳጊዎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመገንባት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ጥረት ለመደገፍ እያበረከቱ ላሉት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይም ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር በበኩላቸው ከተማ መስተዳድሩ ለትምህርት ቤት ምገባ ከፍተኛ ትኩረት ስጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም ተወካይ ሚስተር ኤልቪስ ኦድኬ ኢትዮጵያ በዚህ አመት በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ተጠቃሚ በማድረግ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ መሆኑዋን ጠቅሰው በቀጣይም እ.አ.አ. በ2030 ሁሉንም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የምገባ መርሃ ግብር ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራች ያለችው ስራ ስኬታማ እንዲሆን ተቋማቸውም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጽዋል፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳደር ትምህርት ቢሮ፥ የሴክተር መ/ቤቶች ተወካዮችና አመራሮች፥ ሌሎችም ባለድርሻና አጋር አካላት እንዲሁም የዴሬደዋ ከተማ መስተዳደር አመራሮች፥ የአከባቢው ማህበረስብ ተወካዮች የተሳተፋ ሲሆን ስኬታማ የትምህርት ቤት ምገባ ስራዎች ተጎብኝተዋል ።
በአፍሪካ 9ኛው በኢትዮጰያ አምስተኛው የትምህርት ቤት ምገባ ቀን " ለሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ ለተሻለ ትውልድ ግንባታ!!" በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበዓሉ ላይ ተገኝተው የትምህርት ቤት ምገባ ወጪ ሳይሆን በመጪው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ የሚደረግ አዋጭና ዘላቂ የሰብዓዊ ልማት ኢንቨስትመንት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መርሃ-ግብሩ በአግባቡ ከተተገበረ የልጆችን አካላዊና አዕምሮኣዊ ዕድገት በማፋጠንና ጤንነታቸውን በመጠበቅ የተማሪዎችን የትምህርት ውጤታማነት እንዲሻሻል በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የትምህርት ቤት ምገባ እንደሃገር በመንግሰት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ያለና ከ6.2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የመንግስት አካላት፣የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ታዳጊዎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመገንባት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ጥረት ለመደገፍ እያበረከቱ ላሉት አስተዋጽኦ አመስግነው በቀጣይም ድጋፋቸውን ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር በበኩላቸው ከተማ መስተዳድሩ ለትምህርት ቤት ምገባ ከፍተኛ ትኩረት ስጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም ተወካይ ሚስተር ኤልቪስ ኦድኬ ኢትዮጵያ በዚህ አመት በትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ተጠቃሚ በማድረግ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ መሆኑዋን ጠቅሰው በቀጣይም እ.አ.አ. በ2030 ሁሉንም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የምገባ መርሃ ግብር ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራች ያለችው ስራ ስኬታማ እንዲሆን ተቋማቸውም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጽዋል፡፡
በክብረ በዓሉ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳደር ትምህርት ቢሮ፥ የሴክተር መ/ቤቶች ተወካዮችና አመራሮች፥ ሌሎችም ባለድርሻና አጋር አካላት እንዲሁም የዴሬደዋ ከተማ መስተዳደር አመራሮች፥ የአከባቢው ማህበረስብ ተወካዮች የተሳተፋ ሲሆን ስኬታማ የትምህርት ቤት ምገባ ስራዎች ተጎብኝተዋል ።
Mar 01, 2024 76
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች 128ኛውን የአድዋ ድል በዓል በተለያዩ ሁነቶች አከበሩ፡፡

«ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!»በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ128ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀልና ሊሎች መርሃግብሮች አክብረዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት ችቦ እና አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች በሚገባ ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል እንደሃገር የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሆነው አድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተመረቀበት የሚከበር በመሆኑ ድሉን ድርብ ያደርገዋልም ብለዋል
ሰንደቅ ዓላማ በጋራ የመስቀል መርሃ ግብሩን ተከትሎ በማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከአባቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡
በውይይቱ የማጣቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊው አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው የአድዋ ድል ቀደምት አባቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት በማስከበር ያቆዩን መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
«ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!»በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ128ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች ሰንደቅ አላማ በጋራ በመስቀልና ሊሎች መርሃግብሮች አክብረዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት ችቦ እና አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች በሚገባ ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል እንደሃገር የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሆነው አድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተመረቀበት የሚከበር በመሆኑ ድሉን ድርብ ያደርገዋልም ብለዋል
ሰንደቅ ዓላማ በጋራ የመስቀል መርሃ ግብሩን ተከትሎ በማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከአባቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አመላክተዋል፡፡
በውይይቱ የማጣቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊው አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው የአድዋ ድል ቀደምት አባቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት በማስከበር ያቆዩን መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
Feb 29, 2024 67
National News

የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል!

የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል።
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እኤአ አቆጣጠር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከበር በወሰኑት መሠረት የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በየአመቱ ማርች አንድ በህብረቱ አባል ሀገራት አስተናጋጅነት እየተከበረ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡
 
በዚህ አመትም 9ኛው የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን "አካታችና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ላይ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይገባል” በሚል መሪ ቃል ነገ በድሬደዋ ከተማ ይከበራል፡፡
 
በኢትዮጵያ ከ6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሲሆኑ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር መጠነ ማቋረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ የሁሉንም ዜጋ ትብብር ይሻል!
የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን ነገ የካቲት 22/2016 ዓ.ም ይከበራል።
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እኤአ አቆጣጠር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከበር በወሰኑት መሠረት የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በየአመቱ ማርች አንድ በህብረቱ አባል ሀገራት አስተናጋጅነት እየተከበረ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡
 
በዚህ አመትም 9ኛው የአፍሪካ ትምህርት ቤት ምገባ ቀን "አካታችና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ላይ መዋዕለ ንዋይን በማፍሰስ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይገባል” በሚል መሪ ቃል ነገ በድሬደዋ ከተማ ይከበራል፡፡
 
በኢትዮጵያ ከ6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ ሲሆኑ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር መጠነ ማቋረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ የሁሉንም ዜጋ ትብብር ይሻል!
Feb 29, 2024 67
National News

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን  ዲገሉ ጢጆ ወረዳ ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሚኒስትር ደኤታዋ ክብርት ወይዘሮ አየለች እሸቴ  በአርሲ ዞን  ዲገሉ ጢጆ  ወረዳ በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሠረት ድጋይ አስቀምጠዋል ።

በመርሃ-ግብሩ ላይ  የኦሮሚያ ክልል የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ ጨምሮ የሠዎች ለሠዎች ድርጅት ተወካይ እና ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሀገሪቱን  በአለም ተወዳዳሪ ማድረግ የሚቻለው  በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በግብረገብ የታነፁ ተማሪዎችን ማፍራት ሲቻል መሆኑን አንስተው ለዚህም ጠንክሮ መስራት ይባል ነው ያሉት፡፡

አክለውም የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው በትምህርት ቤት ምቹ የትምህርት ከባቢን መፍጠር ሲቻል መሆኑን ያነሱት የትምህርት ሚኒስትሩ ለዚህም ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ስራዎች እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የሠዎች ለሠዎች ግብረ ሰናይ ድርጅትም ትምህርት ቤቱን ለመገንባት ላደረገው ድገፍ ምስጋና አቅርበዋል።

የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ  ትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ስብራትን ለመጠገን ከሚያደረገው ጥረቶች አንዱ የሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ እንዲጀመር የትምህርት ሚኒስቴርና ሰዎች ለሰዎች  ላደረገው አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡

የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስኪጠናቀቅም ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

ግንባታውን የሚያከናውነው የሠዎች ለሠዎች ድርጅት ተወካይ አቶ ይልማ በበኩላቸው ድርጅቱ የትምህርት ዘርፉን በመደገፍ ረገድ በርካታ ስራዎችን እየሠራ ሲሆን 20 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር መግባባቱን አንስተው ዛሬ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠው አንዱ መሆኑን አንስተዋል።

የግንባታው አጠቃላይ ወጪ ሰዎች ለሰዎች ግብረ-ሠናይ ድርጅት  የሚሸፈን ሲሆን እስከ መስከረም  ይጠናቀቃልም ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻልና ለመቀየር ትምህርት ለትውልድ ንቅናቄን ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንዳለ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሚኒስትር ደኤታዋ ክብርት ወይዘሮ አየለች እሸቴ  በአርሲ ዞን  ዲገሉ ጢጆ  ወረዳ በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሠረት ድጋይ አስቀምጠዋል ።

በመርሃ-ግብሩ ላይ  የኦሮሚያ ክልል የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ ጨምሮ የሠዎች ለሠዎች ድርጅት ተወካይ እና ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሀገሪቱን  በአለም ተወዳዳሪ ማድረግ የሚቻለው  በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በግብረገብ የታነፁ ተማሪዎችን ማፍራት ሲቻል መሆኑን አንስተው ለዚህም ጠንክሮ መስራት ይባል ነው ያሉት፡፡

አክለውም የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው በትምህርት ቤት ምቹ የትምህርት ከባቢን መፍጠር ሲቻል መሆኑን ያነሱት የትምህርት ሚኒስትሩ ለዚህም ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ስራዎች እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የሠዎች ለሠዎች ግብረ ሰናይ ድርጅትም ትምህርት ቤቱን ለመገንባት ላደረገው ድገፍ ምስጋና አቅርበዋል።

የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ  ትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ስብራትን ለመጠገን ከሚያደረገው ጥረቶች አንዱ የሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ እንዲጀመር የትምህርት ሚኒስቴርና ሰዎች ለሰዎች  ላደረገው አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡

የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስኪጠናቀቅም ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

ግንባታውን የሚያከናውነው የሠዎች ለሠዎች ድርጅት ተወካይ አቶ ይልማ በበኩላቸው ድርጅቱ የትምህርት ዘርፉን በመደገፍ ረገድ በርካታ ስራዎችን እየሠራ ሲሆን 20 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር መግባባቱን አንስተው ዛሬ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠው አንዱ መሆኑን አንስተዋል።

የግንባታው አጠቃላይ ወጪ ሰዎች ለሰዎች ግብረ-ሠናይ ድርጅት  የሚሸፈን ሲሆን እስከ መስከረም  ይጠናቀቃልም ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻልና ለመቀየር ትምህርት ለትውልድ ንቅናቄን ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንዳለ ይታወቃል።

Feb 23, 2024 66
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰላ ከተማ በባለሀብት ተሳትፎ ለሚገነባው አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በባለሀብት ተሳትፎ ለሚገነባው የመጀመሪያው አዳሪ ትምህርት ቤት የመሠረት ድጋይ አስቀምጠዋል ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ እና ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ መረሃ ግብር ወቅት ደረጃቸውን የጠበቁ የትምህርት ተቋማትን መገንባት ብቁ የሆነ የሰው ኃይልን ለማፍራት የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው ትምህርትን ለሁሉም ማድረስ ሲቻል ነው ያሉት ሚኒስትሩ በገጠርም ሆነ በከተማ ሁሉም ዜጋ ጥሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ከተጀመረ ጀምሮ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተው ይህ ትምህርት ቤት በግለሰብ ደረጃ የሚገነባ የመጀመሪያው አዳሪ ትምህርት ቤት ነውም ብለዋል።
እንዲህ ዓይነት ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርትን ለመስጠት አስተዋጽአቸው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ በበኩላቸውበትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ትምህርት ሚኒስቴርና ክልሉ ላደረገው ጥሪ ባለሀብቱ አቶ ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ ለሠጡት ምላሽ አመስግነዋል።
የትምህርት ሥራ በመንግስት ብቻ የሚሠራ አይደለም ያሉት ዶ/ር ቶላ ህብረተሰቡ አሁንም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
በአቶ ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ የሚገነባው አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ሲጠናቀቅ ለአቅመ ደካማ ወላጅ አልባ ህፃናት አገልግሎት የሚሠጥ መሆኑም ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ከተጀመረ ጀምሮ በሀገር ደረጃ እስካሁን ሦስት ሺ የሚደርሱ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን ከ11 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች ደግሞ እድሳት የተደረገ ላቸው መሆኑም በመድረኩ ተገልጿል

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በባለሀብት ተሳትፎ ለሚገነባው የመጀመሪያው አዳሪ ትምህርት ቤት የመሠረት ድጋይ አስቀምጠዋል ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ እና ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ መረሃ ግብር ወቅት ደረጃቸውን የጠበቁ የትምህርት ተቋማትን መገንባት ብቁ የሆነ የሰው ኃይልን ለማፍራት የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው ትምህርትን ለሁሉም ማድረስ ሲቻል ነው ያሉት ሚኒስትሩ በገጠርም ሆነ በከተማ ሁሉም ዜጋ ጥሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ከተጀመረ ጀምሮ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተው ይህ ትምህርት ቤት በግለሰብ ደረጃ የሚገነባ የመጀመሪያው አዳሪ ትምህርት ቤት ነውም ብለዋል።
እንዲህ ዓይነት ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርትን ለመስጠት አስተዋጽአቸው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ በበኩላቸውበትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ትምህርት ሚኒስቴርና ክልሉ ላደረገው ጥሪ ባለሀብቱ አቶ ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ ለሠጡት ምላሽ አመስግነዋል።
የትምህርት ሥራ በመንግስት ብቻ የሚሠራ አይደለም ያሉት ዶ/ር ቶላ ህብረተሰቡ አሁንም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
በአቶ ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ የሚገነባው አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ሲጠናቀቅ ለአቅመ ደካማ ወላጅ አልባ ህፃናት አገልግሎት የሚሠጥ መሆኑም ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ከተጀመረ ጀምሮ በሀገር ደረጃ እስካሁን ሦስት ሺ የሚደርሱ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን ከ11 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች ደግሞ እድሳት የተደረገ ላቸው መሆኑም በመድረኩ ተገልጿል
Feb 22, 2024 72

Our Ministers

MINISTER

H.E Pro. Birhanu Nega

Ministry of Education

STATE MINISTER

H.E Mrs. Ayelech Eshete

General Education

STATE MINISTER

H.E Ato Kora Tushune

Higher Education

Organization structure

This is The Main Ministry Organization Structure Chart

General Education

Curriculum Development Executive

Head, Language and Co-curricular Education Curriculum Desk

Head, Social Science Education Curriculum Desk

Head, Natural Science Education Curriculum Desk

Head, Career and Technical Education Curriculum Desk

Teachers’ and Educational Leaders’ Development Executive

Head, Teachers’ and Educational Leaders Development Desk

Head, Education Language Development Desk

Head, STEAM DESK

Educational Program and Quality Improvement Executive

Head, Education Programs and Quality Improvement Desk

Head, Pastoralist and Special Needs Education Desk

Head, Education Infrastructure and Service Desk

Head, General Education Inspection Desk

Adult and Non-formal Education Programs Executive

Head, Adults’ Basic Education Desk

Head, Non-Formal and Lifelong Education Programs Desk

Higher Education

Academic Affairs Executive

Head, Competency and Quality Improvement Desk

Head, Curriculum and Programs Desk

Head, Teachers’ and Students’ Development Desk

Head, Private Higher Education Institutions Service Desk

Research and Community Engagement Executive

Head, Research and Extension Desk

Head, Research Ethics Desk

Head, Institutional Linkage and Technology Transfer Desk

Head, Community Engagement and Indigenous Knowledge Desk

Governance and Infrastructure Executive

Head, Administration Affairs Desk

Head, Institutional Structure and Leadership Desk

Head, Infrastructure and Input Desk

Head, Scholarship and Internationalization Desk

ICT and Digital Education Executive

Head, Education Multimedia Program Development Desk

Head, School Net ICT Desk

Head, Education Media Studio Operation and Administration Desk

Head, Network Technical Desk

Head, Network Operation Desk